ከአቶ ኃይለማርያም መጠበቃችን ስህተት ነበር

ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ PM Hailemariam Desalegnግርማ ካሳ
በሕገ መንግሥቱ መሰረት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰብሳቢ ናቸው። የጦር ኃይሎች ኤታ ማጆር ሹምን፣ ተቀዳሚ ጠቅላይ ሚኒስትርን፣ የሚኒስቴር ካቢኔዎችን፣ የፌደራል ፖሊስ አዛዦችን ... የመሾምና የመሻር ሙሉ ሥልጣን አላቸው። ፓርላማውን በትነው አዲስ ምርጫ መጥራትም ይችላሉ። ፓርላማው በፈለገ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትሩን አውርዶ፣ ሌላ መሾም ይችላል። ጠቅላይ ሚኒስትሩም ተጠሪነታቸው ለፓርላማው ብቻ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሽብርተንነት ስም የህዝብ መብቶችን ማፈን ይቁም!

ቅዱስ ዮሃንስ

ፀረ -ሽብርተኝነት ለአምባገነኖች ሁለት ጥቅም ያስገኝላቸዋል። አንደኛ በፀረ- ሽብርተኝነት ስም ከምዕራባውያን ኃያላን ጎን በአጋርነት በመቆማቸው በጥሬ ገንዘብም ሆነ በዓይነት (ለምሳሌ በመሣሪያ፣ በፖለቲካ ድጋፍ) ዳጎስ ያለ ጥቅም ያገኛሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ተዋርደን አንቀርም!

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት (የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር) Eng.Yilkal Getnet Chairman of Blue Party.ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
(የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር)

ሳውዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ እያደረሰች ያለውን ግፍና በደል በሰላማዊ ሰልፍ ለመቃወም ፓርቲያችን በወሰነው መሰረት ለሚመለከተው ክፍል አሳውቀን ነበር። መቼም ህዝባችን በጭቆና ውስጥ ስለኖረ በመብቱና በግዴታው መሀል ያለውን ድንበር በውል ካለመረዳቱ የተነሳ ሰልፉ እንዲደረግ ስለመፈቀዱ በተደጋጋሚ ስንጠየቅ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ውለታ ተካደ፣ ማሩ ተቆረጠ

ዓለማየሁ ዲባባ

የሳዑዲ ሕዝቦች በአንድ የታሪክ ዘመናቸው በኃይማኖት ልዩነት እርስ በእርሳቸው ተፋጅተው ወደ ኢትዮጵያ በተሰደዱ ወቅት ተቀብለናቸው አኑረናል፣ አስጠልለን መግበናል፣ አልብሰን አርዘናል። ከለላ እና ጥበቃ ሰጥተናቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሞት፣ ወያኔና "እኛ"

ፊልጶስ
የግፍ ጽዋው ሞልቶ፣ ...
ሞልቶ፣ ... ሞልቶ ፈሶ
ሰው መባል በሰው፣ ስዕብናችን አሶ
ከ'ጥናፍ - እስከ - አጥናፍ፣ ደማችን "'ረክሶ"፤
ውቅያኖስ፣ ባህሩን፣ ወንዙን አደፍርሶ
እዩት ይ'ጣለላል፣ አስፋልቱን አልብሶ።
ግን እኮ፣ ... እንኳ' ደም
ውኃ ፈሶ፣ አይቀርም
ይዘገያል እንጂ፣ በሰፈሩት ቁና፣ መሰፈር አይቀርም።
"ዓለም የም'ጠፋው፣ ሰይጣናዊ ምግባር በሚፈጽሙ ሳይሆን፤ ምንም ሳያደርጉ ቀጭ ብለው በሚመለከቷቸው ሰዎች ነው።" /አልበርት አነስታይን/

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያዊ ዋጋው ስንት ነው?

ተመስገን ደሳለኝ (አዲስ አበባ)

የዚህ ፅሁፍ ማጠንጠኛ የፖለቲካ አመለካከትን መተቸት አይደለም፤ ከዋና ዋና  ገራዊ አ ንዳዎች ወረድ ያሉ የጉልበታሙን ስርዓት የሥራ አፈፃፀሞችን ማብጠልጠልም አይደለም፤ የተቀናቃኝ ፓርቲዎችን ስንክሳር መንቀስም… አይደለም፡፡ ኢትዮጵያዊ (አል- በሽ) መሆን ለፈተና፣ ለመከራ፣ ለሰቆቃ… መዳረጉ የወለደው ብሶት እንጂ፤ መመረር-ማምረር ነው፡፡ …ይህ የእኛ ዕጣ ፈንታ የሆነበትን ምስጢር መመርመር ነው፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እስቲ የነበርነው እንጻፍ! የኢሕአፓ ረጅም ትግል

ኢያሱ ዓለማየሁ

የኢሕአፓ 41 ዓመት መራራና ረጅም ትግል ረጅም ትግስትን ጠይቋል። አያሌ ፈተናዎችን ተቋቁሞና አልፎ ዛሬም ህልውናውን ጠብቆ በትግሉ ሜዳ ላይ መገኘቱ በቅድሚያ የአባላቱታሪክን ገርተውና ጽፈዋት ያለፉትም ሆነ በሕይወት ያሉትን ጽናትና ቆራጥነትየሚመለከት ነው። ኢሕአፓን ለመመስረትና መስርቶም ለማታገል በተደረገው ትግል በታሪክ አጋጣሚ ዋና ተካፋይ ሆኜ በመቆየቴ የሚሰማኝ ደስታና ክብርም ወደር የለውም። ሀቁ ይህ ድርጅት ከቶም ባልተመሰረተ የሚሉት ጠላቶች እንደ ነበሩትና እንዳሉት ሁሉ (በአብዛኛው ከስርዓቶቹ ጋር የተያያዙ) ቤዛችን ነው፣ የወኔያችን መከሰቻ ነው፣ የሀገር አለኝታችን ነው ድርጅታችን ነው የሚሉ ደሞ ብዙዎች ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ፣ በህዳርና በ… ሁልጊዜ አስታውሳለሁ!!

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

የህዳር ወር በኢትዮጵያውያን በአሰቃቂነቱ ሁልጊዜ ሲታወስ ይኖራል፡፡

እ.ኤ.አ ኖቬምበር 2013 ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በቃላት ለመግለጽ በሚዘገንን መልኩ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ ሰቆቃ የተፈጸመበት ወር ነው፡፡ ላለፉት ጥቂት ዓመታት በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ፣ በሚሰሩና የፖለቲካ ጥገኝነት ለመጠየቅ ጥረት በማድረግ ላይ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ ስልታዊ የሆነ ጥቃት ሲሰነዘር ቆይቷል፡፡ እንዲያውም በግል በሚኖሩበት ቤት እምነታቸውን በማራመዳቸው ብቻ ኢትዮጵያውያኑ/ቱ ዜጎች ላይ የወንጀል ድርጊት ተፈጽሞባቸዋል፣ እንዲጋዙም ተደርጓል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወደ ተግባር (ከአንተነህ መርዕድ እምሩ)

ኢትዮጵያውያን እንደ አሁኑ ተገፍተን ገደል ጠርዝ የቆምንበት ጊዜ ያለ አይመስለኝም። እስከ አሁን ትንንሽ መሸሻ ስለነበረን ፍርሃታችንን እንኳን ከሰው ከራሳችንም ደብቀን ስናፈገፍግ ኖረናል። ፈሪነታችንን ባባቶቻችን ጀግንነት፣ ውርደታችንን ባባቶቻችን ኩራት እያለበስነው መጓዝ የማያዛልቅ ለመሆኑ ከሰሞኑ የበለጠ ምስክር ምን አለና።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ