የመጨረሻው ሱባኤ

ሙሉነህዮሃንስ (ከሲያትልዋሽንግተን)

የፍልሰታ ልደታ ቀን 2005 ዓ.ም. ተጻፈ
ክፍል አንድ፡- ንግርት፣ የመጨረሻው መመሪያ ሱባኤና የመንግስት ትንቅንቅ

በታላላቅ የበቁ የቤተ-ክርስቲያን አባቶች ዘንድ ዘመን የተቆጠረለት የኢትዮጵያን መጻኢ እድል የሚተነብይ ጥንታዊ ንግርት አለ። ኢትዮጵያ እግዚአብሔርን በካዱ ጨቋኝ መንግስታት ለአርባ አመታት ወድቃ እንደምትገዛ በታላላቆቹ የኢትዮጵያ ገዳማት አባቶች በለሆሳስ ሲነገር ከርሟል። ይህ ዘመን የሚቆጠረው ጃንሆይ ከተፈናቀሉበት ዘመን  ምሮ ነው። ይህም ሲሰላ መነሻው 1966 ዓ.ም. መሆኑ ነው። አዎን አርባ አመት ከዛ ላይ ስትጨምሩ የዘመን ባቡር በፍጥነት የፊታችን መስከረም 2006 ዓ.ም. ላይ ያደርሰናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግፉዓን ዕድሜ ምን ያህል ይረዝማል?

(ተመስገንደሳለኝ)

…‹‹የጣር ቀጠሮው ስንት ነው
ለሰው ልጅ ሰው ለምንለው
ላይችል ሰጥቶት ለሚያስችለው
ስንት ቀን ነው? ስንት ሌት ነው?...››
(ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን ‹‹እሳት ወይ አበባ›› የግጥም መድብል)
እነሆም ለቅስቀሳ ሳይሆን፣ አንተንም እራሴንም እወቅስ ዘንድ ብዕሬን እንዲህ አነሳሁ፡- ‹‹ ገሬ መከታዬ፣ መኩሪያዬ…›› ከምትላት እናት ኢትዮጵያ ምንድር ነው የምትፈልገው? …ዳቦ፣ ማህበራዊ ፍትህ፣ ፖለቲካዊ ነፃነት፣ ቤት መስራት፣ መማር-አለመማር፣ መደገፍ-መቃወም፣ መተኛት-መነሳት፣ ፈጣሪን ማምለክ-መካድ፣ መስራት-አለመስራት፣ መምረጥ-አለመምረጥ፣ አደባባይ መዋል፣ ሰፈር መዋል፣ መደራ ት-አለመደራ ት፣ ማልቀስ-መሳቅ፣ መፃፍ፣ መናገር፣ መጮኽ-መመሰጥ፣ የግል መብት፣ የቡድን መብት?
ይህ ይሆን ዘንድ ከወዴት ትሻለህ? …ከሙት መንፈስ፣ ከውርሱ ድንዛዜ፣ ከሰማይ፣ ከምድር፣ ከፀሐይ፣ ከጨረቃ፣ ከርዕዮተ-ዓለም ወይስ….?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"የአሲምባ ፍቅር" - መጽሃፍ ቅኝት

 በክንፉአሰፋ

 "የአሲምባ ፍቅር" - መጽሃፍ ቅኝት
በክንፉ አሰፋ
ደራሲ፣ ካሕሳይ አብርሃ ብስራት
ብዛት፣ 446 ገጾች
በተስፋዬ ወልደዮሃንስ አዲስ አበባ ታትሞ የተሰራጨ
* ከስር በስእሉ እንደሚታየው ኢሲምባ 3250 ሜትር ከፍታ ላይ በትግራይ ውስጥ ያለ ተራራ ነው። አሲምባ በዚህ ከፍታው ሳቢያ ሌሊት ላይ በጉም ይሸፈናል። አሲምባ "ቀይ አንባ" ማለት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጴጥሮሳዊነት

/መሰፍን/ማርያም

ቀደምሲል « እግዚአብሔርና እኛ» በሚለው ርዕስ ስር የተነገረውን አንዳንድ ሰዎች ሌላ ትርጉም በመስጠት ጸረሃይማኖት ሊያስመስሉት ይሞክሩ ይሆናል። አይደለምእንዲያውም ሃይማኖትንና ሃይማኖተኛነትን የሚያጸናነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ምንም ዓይነት ሃይማኖት ቢኖረው ለእግዚአብሔር ያለው ፍቅርና በእግዚአብሔርም ላይ ያለው እምነት ብርቱ ነው።ይህንን ከመገንዘብ የተነሳና በዚያው ፍቅርና እምነት ላይ የተመሠረተ ስለሆነ በምንም መንገድ ጸረ ሃይማኖት መስሎ ሊታይ አይገባም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከ“ሙስና”ው ክስ በስተጀርባ

(ተመስገን ደሳለኝ)

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ለትንተና አዳጋች መሆኑን የሚናገሩ ምሁራን መከራከሪያቸው ፖለቲከኞቹ ከርዕዮተ-ዓለም ይልቅ ‹‹ሴራ››ን ማስቀደማቸውን በመጥቀስ ነው። በርግጥም አብዛኛው የፓርቲዎቹ የአመራር አባላት ከክህሎት እና ርዕዮተ-ዓለም መራቀቅ ይልቅ በዘልማዱ ፖሊቲካ የተካኑ ናቸው፡፡ በተለይም የ1966ቱ ‹‹አብዮት›› ያሰረፀው የ‹‹ፓርቲ ፖለቲካ›› የተደራ ‹‹ሴራ›› ምን ያህል ኩነትንም ታሪክንም መቀየር እንደሚችል አሳይቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"አላዋቂ ሳሚ ንፍጥ ይለቀልቃል"

አርኣያ ጌታቸው አርኣያ ጌታቸው 

2005 ዓ.ም. ከ1998 ዓ.ም. በኋላ በተግባር ሊታይ የሚችል የፖለቲካ እንቅስቃሴ የታየበት አመት ነው ብል የተሳሳትኩ አይመስለኝም። በተለይ በግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. የሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ምንአልባትም ወደኋላ ይጓዝ የነበረውን የሀገር ውስጥ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ከማስቆም በዘለለ ወደፊት እንዲጓዝ ያደረገው ይመስለኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሚሊዮኖች-ድምጽ-ለነፃነት ዘመቻ የዜጎችን ፊርማዎች ለመሰብሰብ

ግርማ ሞገስ Girma Mogesግርማ ሞገስ

የዜጎችን ፊርማዎች ማሰባሰብ የብዙ መቶ አመቶች ታሪክ ያለው ሰላማዊ ትግል ነው። የሚሊዮኖች-ድምጽ-ለነፃነት ዘመቻ አንዱ ግብ በኢትዮጵያ ሽብር ህግ ላይ ዜጎች ያላቸውን አቅዋም በፊርማቸው እንዲገልጹ ማድረግ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመንግሥትን ስም ማጥፋት ማለት የክቡርነታቸውን…?

/መሰፍንወልደማርያም

ስም ምንድን ነው? መታወቂያነው፤ መጠሪያነው፤ ስም ማጥፋት ሲባል ስም አለ ማለትነው፤ ከስምም አልፎ የገነነ ስም አለ ማለት ነው፤ ስለዚህም ሊጠፋ የሚችለው የገነነ ስም ሲኖር ብቻ ነው ማለት ነው፤ ደራርቱ ቱሉ፣ ፋጡማ ሮባ፣ ኃይሌ ገብረሥላሴ የገነኑ ስሞች ናቸው፤ አንድ ሰው እነዚህን የገነኑ ስሞች አጠፋህ ቢባል ሊገባን ይችላል፤ ዘለቀ ወርዶፋ፣ አየለ ተከስተ ስማቸው ጠፋ ቢባል፣ መጀመሪያ የሚቀርበው ጥያቄ እነማን ናቸው? ዱሮስ የገነነ ስም ነበራቸው ወይ? የሚል ይሆናል፤ ስለዚህ መሰላሉን ያልወጣውን ሰው ውረድ ቢሉት ትርጉም የለውም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብርቱ ሰው! (The Iron Man)

ከተመስገን ደሳለኝ

ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ

…አራት ኪሎ በሚገኝ አንድ ካፍቴሪያ ከጓደኞቼ ጋር የደራ ወግ በመያዜ፣ የእጅ ስልኬ የ‹‹መልስ ስጠኝ›› ጩኸቱን ደጋግሞ ሲያሰማ ልብ አላልኩትም፤ እናም ጮኾ ጮኾ ሲጨርስ፣ እንደገና ይምራል፡፡ ይኼኔ ጥሪውን እንዳላስተዋልኩ የተረዳው ጓደኛዬ ወደ ስልኩ ሲያመላክተኝ፣ ቁጥሩን አየሁት፤ አውቀዋለው፡፡ የእስክንድር ነጋ ባለቤት የጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል ነው፤ አነሳሁት፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ