ዘራፊ ሚሊየነሮች

ሉሉ ከበደ (ጋዜጠኛና ደራሲ)

ውድ አንባቢያን ወደ ዋናው ጉዳይ ከመሄዴ በፊት ልጠቁም የምፈልገው ነገር የማቀርባቸውን ጽሁፎች በተመለከተ የምትጽፉልኝን አስተያየቶች፤ ትችቶችን አጠቃለው ሁሉንም በጥሞና አነባቸዋለሁ። እናም ሁላችሁንም ከልቤ ሳላመሰግን አላልፍም። ትችት ያስተምራል። የድጋፍም ሀሳብ ያስተምራልም ያበረታታልም። ሁለቱም እኩል ይጠቅማሉ። ወደፊት ከምትልኩልኝ መልሶች አለፍ አለፍ እያልኩ አጠር አጠር ያሉትን ሁለቱን ላንባቢያን አቅርቤ ወደምናገረው ነገር አልፋለሁ። ከዛሬ ልጀምርና “አያልቅበት .. “ ለሚለው ከደረሱኝ አስተያየቶች ሁለቱን ተመልከቱና ወደ አቅርቦቱ እንሂድ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከመለስ ወደ “መለሶች”

በተመስገን ደሳለኝ

እንደ መነሻ

በ1983 ዓ.ም. ወርሃ ግንቦት መንግስታዊ ስልጣን በሃይል የተቆጣጠረው ኢህአዴግ፣ ከጥቂት ወራት በኋላ ሃያ ሁለተኛ ዓመቱን ይደፍናል። በእነዚህ አመታት አገዛዙ ያነበረውን ስርዓት በሶስት የዘመን ክፍፍሎች (Historical Periodization) ወይም ገፅታዎች ከፍለን (በጊዜ እና በግለሰቦች ላይ በተመሰረተ መስፈርት) ማየት እንችላለን። ከ1983 እስከ 1993 ዓ.ም-‹‹ቡድናዊ››፣ ከ1993-2004 ዓ.ም-‹‹ግለሰባዊ›› እና ከ2005…? ዓ.ም-‹‹ቡድናዊ›› በሚል። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዐረብ ሀገራት ያሉ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች በቤት ሠራተኛ ንግድ ላይ ተሰማሩ

ሔለን ዘውዱ አየለ

በኩዌት፣ በሳዑዲ ዓረቢያና በጅዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የሰው ኃይልን በርካሽ ዋጋ ሊያቀርብ እንደሚችል በአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ማስታወቂያ እያስነገረ ነው

ሰው በፈለገበት ቦታና አገር የመዘዋወር መብቱ በሕገ መንግሥቱ ተረጋግጦለታል። በኮንትራት በቤት ሠራተኝነት ወደ አረብ አገሮች የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን የሚደርስባቸው በደል ከጊዜ ወደ ጊዜ መባባሱ ይሰማል። ኢትዮጵያውያኑ ላይ ከፍተኛ የሆነ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት እየደረሰ ነው። ለዚህም በዋነኛነት ማሳያ የሚሆነው በተለያዩ የዓረብ አገሮች በቤት ሠራተኛነት በሚሄዱት እህቶቻችን ላይ የሚታየው የሞት፣ የአካል መጉደል፣ የመደፈርና ያለደመወዝ ማባረር ጥቂቶች ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሰብአዊ መብትና መንግሥታዊ ግፊት በኢትዮጵያ (2012)

ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም / ትርጉም ነጻነት ለሃገሬ

በዲሴምበር 2008 ላይ በኢትዮጵያ የ”ለውጥ የሌሽ ዓመት” በማለት እንጉርጉሮ መሰል መልእክት ጽፌ ነበር።

2008 የ2007፤ 2006፤ 2005፤ 2004 ቅጂ ነበር … በየቀኑ ኢትዮጵያዊያን ሲነቁ ልክ እንደተሰበረ የሙዚቃ ሸክላ ባለፈው የሕይወት ስቃያቸው ድግግሞሽ መከራ ውስጥ በመዳከር ነበር የሚገኙት። እያንዳንዱ አዲስ ቀን ካለፈው የወረሰውን ይዞ ነበር የሚመጣው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ተው ስማኝ ሀገሬ ...

አቡ ዘኪያ ከምድረ-አናቶሊያ

ኢሕአዴግ በሀገራችን ዴሞክራሲ ማስፈኑንና ሕገ-መንግሥታዊ ስርዓት መዘርጋቱን ሌት ተቀን ይተርክልናል። እውነታው ግን ሀገራችን በ81 ዓመት የሕገ-መንግሥት ታሪኳ ውስጥ አንድም ጊዜ እደግመዋለሁ አንድም ጊዜ ሕገ- መንግሥታዊ ስርዓት ለማየት አልመታደሏ ነው። የኢሕአዴግ አብዮታዊ ዴሞክራሲ ፀረ-ዴሞክራሲ አብዮት ነው። ኢሕአዴግ ሕገ-መንግሥቱን የወረቀት ላይ ነብር አድርጎታል። ተቃዋሚዎችን በፀረ-ሕገ መንግሥታዊነት የሚነቅፈው ኢሕአዴግ የሕገ-መንግሥቱ ቀንደኛ ባላንጣ ነው ...

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዛሬ አበባዎች

ኤፍሬም እሸቴ

ልጅነት የንጽሕና እና የንፁህ ልብ ዕድሜ ዘመን እንደሆነ በሁሉም ሰው፣ በሁሉም ባህልና እምነት ይታመናል። ይህ እውነት መሆኑን ወላጅ የሆነ ሰው ወይም ለሕጻናት ቅርበት ያለው ሰው ጥናትም ባያደርግ ይረዳዋል። ሁላችንም በልጅነት ዕድሜ ስላለፍን በርግጥም እኛም ምስክሮች ነን። 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመናበብ ጥበብ

ዳኮታ የጥናት ማዕከል

ቁጥራቸው ከአንድ በላይ የሆኑ ሰዎች በተመሳሳይ ጊዜና ሁኔታ ውስጥ የሚያስቡት ተመሳሳይ ወይ ተዛማጅ ሀሳብ። ፍላጎትን ማስማማት። የሌሎችን ሀሳብና ፍላጎት በቶሎ ከመረዳት ጋር ወደሚታይ ተግባር የመቀየር ችሎታ መናበብ ይባላል። መናበብ ጥበብ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የህወሓት የብረት መዳፍ

(ተመስገን ደሳለኝ)

የድህረ-መለስ ዝግመተኛውና መቋጫ ያጣው የፖለቲካ ማዕበል፣ አሁንም አዳዲስ ክስተቶችን ማሳየቱን አላቋረጠም፡፡ ዝነኛው ‹‹የመለስ ራዕይ›› መፈክርም ግንባሩን የታሰበውን ያህል ወደ አንድ ለማሰባሰብ አቅም ያጠረው ይመስላል፡፡ ጥገናዊ ለውጦቹም እንዲሁ አትራፊ መሆን አልቻሉም፡፡ መ ል አራት ኪሎ በሚገኘው የኢህአዴግ ጽ/ቤት ግድግዳ ላይ የተሰቀለው የመለስ ፎቶም ‹‹ሸምጋይ›› አልሆናቸውም፡፡ ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጂጂና ቴዲ፣ እንደ ቦብ ማርሊ እንደ ፌላ ኩቲ

(ክንፉ አሰፋ)

ጃማይካዊውን የጥበብ ሰው ጋሪሰን ሃውክን በመንተራስ አርቲስት ጂጂ እና ቴዲ አፍሮ ሰሞኑን የለቀቁት 'ጀግና አይፈራም … ተስፋ አይቆርጥም'´ ነጠላ ዜማ በብዙዎች አድናቆትን እየተቻረይገኛል። ብዙዎችንም አነቀቅቷል። ሙዚቃው የተለየ ነው፣ የሚያበረታታ እና የሚያነቃቃም ነው። 'ጀግና አይፈራም … ተስፋ አይቆርጥም'! ሙሉውን አስነብበኝ ...

አሜሪካ ከጀግኖች አፍሪካውያን ጎን ትቆማለች ?

ከፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም ከነጻነት ለሃገሬ)

ታሪክ ከጀግኖች አፍሪካውያን ጋር ከወገነ፤ አሜሪካስ ለምን አትወግንም ?

ፕሬዜዳንት ኦባማ አክራ፤ ጋናን በ2009 ሲጎበኙ ሁለት አስቸኳይና አስፈላጊ መልዕክቶችን አስተላልፈው ነበር። ‹‹ታሪክ ከጀግኖች አፍሪካውያን ጋር ወግኗል›› ሲሉ: ለአፍሪካ መሪዎችና ገዢዎች ደግሞ ጠበቅ ያለ መልክት ኣስተላፈው ነበር። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ