ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ምርጫ 2012ና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የሰጡት መግለጫ

PM Abiy Ahmed

ክቡራንና ክቡራት ኢትዮጵያውያን፤

በዘመናዊ የኢትዮጵያ ታሪክ ጎልተው ከወጡ የሕዝብ ፍላጎቶች አንዱ ሕዝብ የሚሳተፍበትና የሚሰማበት የአስተዳደር ሂደት፣ በሌላ አነጋገር ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት የመገንባት ፍላጎት ነው። ይህ ፍላጎት ከዘመን ወደ ዘመን እያደገ፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ ዛሬ ላይ ደርሷል። በዚህ ባለንበት ዘመንና ትውልድ ይህ ፍላጎት እውን ሆኖ ዲሞክራሲያዊ አገር እንድንገነባ ትልቅ ፋይዳ የሚኖረው አንዱ ኩነት ቀጣዩ ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ መሆኑ ግልጽ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከኢዜማ የተሰጠ የአቋም መግለጫ (ሚያዝያ 28 ቀን 2012 ዓ.ም.)

ኢዜማ

የምንሰጠው ሕጋዊና ፖለቲካዊ አማራጭ ከወቅታዊው የኮሮና ወረርሽኝ የሚታደገን፣ አገረ-መንግሥቱን የሚያስቀጥልና ወደ ተረጋጋ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የምናደርገውን ሽግግር የሚያግዝ ሊሆን ይገባል!

ከኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የተሰጠ የአቋም መግለጫ

የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከባድ ጉዳት እያደረሰ እንደሆነ ይታወቃል። ወረርሽኙ በሰዎች ጤና እና ደህንነት ላይ ካደረሰው እና እያደረሰ ካለው ጉዳት ባልተናነሰ የዓለምን እና የአገሮችን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊ እና ፖለቲካዊ መስተጋብሮች እና ሥርዓትን ከባድ አደጋ ውስጥ ከቷል። ወረርሽኙ በአገራችን ኢትዮጵያ እስከካሁን ያስከተለው ጉዳት ከሌሎች አገሮች ጋር ሲነጻጸር አስከፊ የሚባል ባይሆንም የደቀነው አደጋ ግን ከፍተኛ መሆኑ እርግጥ ነው። በሌሎች አገር ከታየው ተሞክሮ አንፃር ወረርሽኙ ድንገት በከፍተኛ ቁጥር ዜጎችን ሊያጠቃ እና የጤና ሥርዓት ቀውስ ውስጥ ሊከተን የሚችልበት አደጋ አሁንም አለ። የጎረቤት አገሮች (ሱዳን፣ ጅቡቲና ሶማሊያ) የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በፍጥነት መዛመት የጀመረበትና በተለይ ከጅቡቲ ጋር ካለን የቀረበ የኢኮኖሚ ትስስር አንፃር በምስራቁ የአገራችን ክፍል ላይ የደቀነው ስጋት ከፍተኛ እንደሆነ ግልጽ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"ሕግን ያላግባብ በመተርጎም የብልጽግናን ሕገወጥ የሥልጣን ዕድሜ የማራዘም እንቅስቃሴ ፍጹም ተቀባይነት" ሕወሓት

TPLF (Tigray People's Liberation Front)

ከሕወሓት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ

የሕወሓት ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ከሚያዝያ 23-25/2012 ዓ.ም በክልላችንና በአገራችን እንዲሁም በንኡስ ቀጣናው የተከሰቱ ፖለቲካዊ ጉዳዮችን በስፋት በመመርመር የውሳኔ ሐሳቦችን አሳልፏል። ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በክልላችን እየተከናወኑ ያሉ የሰላምና የልማት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የክልላችንና የሕዝባችን ድህንነት የመታደግ ሥራዎችን እንዲሁም የኮረናን ወረርሽኝ ለመመከት የተሰሩ ሥራዎች በሚመለከት በዝርዝር የተወያየበት ሲሆን፣ እስካሁን የታዩ ጥንካሬዎችን ጠብቆ ለማቆየትና የታዩ ጉድለቶችን ለማረም የተሰሩ ስራዎችን በመመርመር ውሳኔዎችን አሳልፏል። በክልላችን ያሉ ወይም የሚኖሩ ፈተናዎች ለመመከት አሁንም ወሳኙ ውስጣዊ ጥንካሬያችን መሆኑን በድጋሚ በማረጋገጥ በዚህ ረገድ የተጀመሩ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ስምምነት ላይ ተደርሷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአዲስ ማኅበራዊ ውል የምንደራደርበትና የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥትን የማሻሻያው ጊዜ አሁን ነው!

National Movement of Amhara (NAMA)

ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ለኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ የቀረበ ታሪካዊ አገራዊ ጥሪ!

• ለኢፌዴሪ ጠ/ሚ/ር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ
• ለኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ
• ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
• ለኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት
• ለመላው የአማራ ሕዝብ
• ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝቦች
• ለተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች
• ለዓለም አቀፍና አገር አቀፍ ሚዲያዎች
• በአዲስ አበባ ለሚገኙ ለኢትዮጵያ ወዳጅ አገራት ኢምባሲዎች፣ ሚሲዮኖችና ዓለም አቀፍ ተቋማት
ክቡራትና ክቡራን፣

በመላው ዓለም የተከሰተውን የሳምባ ቆልፍ (ኮቪድ-19) ወረርሽኝን ተከትሎ በኢትዮጵያም አገራዊ የጤናና የማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ችግር መሆኑን በመገንዘብ በመጪው ነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ይካሄዳል ተብሎ ታስቦ የነበረው 6ኛ ዙር አገራዊ ምርጫ በተያዘለት ጊዜ ማካሄድ እንደማይችልና ምርጫውም ላልተወሰነ ጊዜ እንደተራዘመ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማስታወቁ የሚታወስ ነው፡፡ ይህንን ተከትሎ በስልጣን ላይ ያለው መንግሥት በዚህ አመት መጨረሻ የስልጣን ዘመኑ የሚጠናቀቅ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ምን ሊደረግ እንደሚችል በሁላችንም ዘንድ የመወያያ አጀንዳ ሆኖ ሰንብቷል፡፡

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"የኢትዮጵያ የለውጥ ሒደት፣ የቀጣዩ ምርጫ አገራዊ ፋይዳና የተደቀኑ አደጋዎች" የኢዜማ መሪ

ከኢዜማ መሪ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተላለፈ መልዕክት

ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ፤ እንደምን ከረማችሁ
በዛሬው ዕለት እንደ ኢዜማ መሪም ሆነ እንደ አንድ ዜጋ፣ ከኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ጋር በዚህ መልክ ለመገናኘት ምክንያት የሆነኝ ከፊታችን በተደቀነው ምርጫ ላይ ኢዜማን እንድትመርጡ ለመቀስቀስ አይደለም። እሱ ሁሉም የፖለቲካ ድርጅቶች የምርጫው ቅስቀሳ ጊዜ በግልጽ ሲታወጅ የምናደርገው ይሆናል። ይልቁንም ዛሬ ላዋያችሁ የምፈልገው እንደ አገርም እንደ ሕዝብም ልንጋፈጠው የሚገባን ፊት ለፊታችን የተጋረጠ አንድ ትልቅ እውነትን ነው፤ ... ዛሬ በተለያዩ የአገራችን አካባቢዎች የሚከሰቱ አለመረጋጋቶች፣ ግጭቶችና ከዕለት ወደ ዕለት አሳሳቢ እየሆነ የመጣው የሰላም ዕጦት፣ ነገ ደግሞ ምን ይዞ ይመጣ ይሆን የሚል ሥጋት/ጭንቀት አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እየደረሰ ያለውን ወቅታዊ ችግር አስመልክቶ ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሠጠ መግለጫ

Ethiopian Orthodox Synodos

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሠጠ መግለጫ (የካቲት 11 ቀን 2012 ዓ.ም.)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቤተ ክርስቲያኒቱና በምእመናን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር አስመልክቶ ከየካቲት 9 -11 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ ተነጋግሮ በቤተ ክርስቲያናችን በተለያዩ ገዳማትና አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም የቤተ ክርስቲያናችን ተከታይ የሆኑ ምእመናን ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር አስመልክቶ በመነጋገር እና ውሳኔ በማሳለፍ የሚከተለውን መግለጫ አውጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የትግራይ ብልጽግና ፓርቲ ለ45ኛው የካቲት 11 በዓል ያስተላለፈው መልእክት

Ethiopian Prosperity Party

ከትግራይ የብልጽግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት የተላለፈ መልእክት

አኩሪው የትግራይ ሕዝብ የጸረ ጭቆና ተጋድሎና መሥዋዕትነት በከሠሩ ኃይሎች ኣይራከስም ፤ የቡዱናዊ ፍላጎት መጠቀሚያም አይሆንም እጅግ የተከበርከውና ከባድ የሕይወት መስዋእትነትን ጨምሮ ውድ ዋጋ በመክፈልና መራራ ትግል በማካሔድ ለራስህ ብቻ ሳይሆን ለወገኖችህ የሚተርፍ ድል ያስመዘገበከው መላው የትግራይ ሕዝብ እንኳን ለ45ኛው የካቲት 11 በዓልህ በሰላም አደረስህ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ