The first president of Benishangul and Gumuz, Yaregal Ayesheshum

የመጀመሪያው የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ያረጋል አይሸሹም

አቶ ያረጋል አይሸሹም ያረፉት በድንገተኛ ሕመም ነው

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. November 19, 2019)፦ የመጀመሪያው የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ፕሬዝዳንት (ርዕሰ መስተዳድር) አቶ ያረጋል አይሸሹም ትናንት ኅዳር 8 ቀን 2012 ዓ.ም. አረፉ። አቶ ያረጋል በድንገተኛ ሕመም ማረፋቸው ዛሬ ተሰምቷል።

ከቤንሻንጉል ፕሬዝዳንትነታቸው በተጨማሪ የፌዴራል ሕብረት ሥራ ኤጀንሲ ዳይሬክተር በመኾን ሲያገለግሉ መቆየታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል በመኾንም አገልግለዋል።

አቶ ያረጋል በፌዴራል መንግሥት በሙስና ተከሰው ታስረው የነበረ ሲሆን፣ ከእስር ከወጡ በኋላ የተከሰሱት ክስ አግባብ አልነበርም በማለት መናገራቸው አይዘነጋም።

አቶ ያረጋል የቤንሻንጉል ርዕሰ መስተዳድር ኾነው ያገለገሉት ከ1987 - 2002 ዓ.ም. ነው። አቶ ያረጋል 51 ዓመታቸው ነበር። (ኢዛ)

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ