Development Bank of Ethiopia

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ

በአራት ዓመት ውስጥ የተበላሸ ብድሩን 10 በመቶ ለማድረስ አቅዷል

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 27, 2020)፦ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የተበላሸ የብድር መጠኑን ከ40 በመቶ ወደ 34 በመቶ ያወረደ መኾኑን ዛሬ የባንኩ ባለሥልጣን በሠጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

የባንኩ የተበላሸ የብድር መጠን በየዓመቱ ለመቀነስ እቅድ ተይዞ እየተሠራ መኾኑንና በአራት ዓመት ውስጥ ወደ 10 በመቶ ለማድረስ እየሠሩ መኾኑን ገልጸዋል።

ባንኩ አምና 740 ሚሊዮን ብር ኪሳራ አስመዝግቦ የነበረ ሲሆን፤ ዘንድሮ ግን በግማሽ ዓመት ከግብር በፊት ከ950 ሚሊዮን ብር በላይ በማትረፍ ከኪሳራ መውጣቱንም ገልጸዋል። (ኢዛ)

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ