ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ተፈቱ

Ethiopia Zare (ረቡዕ መስከረም 26 ቀን 2003 ዓ.ም. October 6, 2010)፦ ላለፉት 647 ቀናት በቃሊቲ እስር ቤት ታስረው የነበሩት ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ ዛሬ ረቡዕ መስከረም 26 ቀን 2003 ዓ.ም. (ኦክቶበር 6 ቀን 2010 እ.ኤ.አ.) በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር አምስት ሰዓት አካባቢ መፈታታቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።
ለወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ፣ ለልጇ ሕፃን ሐሌ ሚደቅሳ፣ ለእናቷ፣ ለዘመዶች፣ ለወዳጆችዋ፣ እንዲሁም ለደጋፊዎቻቸው በዚህ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ እንኳን ደስ ያላችሁ ትላለች።
ቀሪ ዘገባ ዘግይተን ለማቅረብ እንሞክራለን።



