ለኦነግና ለኦብነግ የእውቅና የምስክር ወረቀት ተሠጠ
ኦነግ ለምርጫ ቦርድ ምስጋና አቀረበ
ኢዛ (ዓርብ ኅዳር ፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. November 15, 2019)፦ ለኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) እና ለኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የእውቅና የምስክር ወረቀት እንደሠጣቸው አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ኅዳር 5 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ እንዳደረገው ለሁለቱ አገር አቀፍ ፓርቲዎች የእውቅና ሰርትፊኬቱን (የፖለቲካ ፓርቲዎች የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት) የሠጣቸው ትናንት ኅዳር 4 ቀን 2012 ዓ.ም. ነው።
ኦነግ የእውቅና ሰርትፊኬቱን ማግኘቱን ተከትሎ በሠጠው መግለጫ፤ በአገሪቱ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ውስጥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እየተጫወተ ላለው ሚና ምስጋና አቅርቧል። (ኢዛ)