አቶ ለማ መገርሳ በመከላከያ ጉዳይ ለመምከር ዋሽንግተን ዲሲ ናቸው
ምክክሩ በኢትዮጵያና በአሜሪካን የሁለትዮሽ የመከላከያ ትብብር ለማጠናከር እንደኾነ ተደምጧል
ኢዛ (ሰኞ ኅዳር ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. December 2, 2019)፦ ከሰሞኑ አነጋጋሪ የኾነ ቃለምልልስ ለአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ የሠጡት የመከላከያ ሚኒስትርና የኦዴፓ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ለማ መገርሳ የመሩት የልዑካን ቡድን ዋሽንግተን ዲሲ መግባቱ ተገለጸ።
አቶ ለማ የመሩት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ወደ አሜሪካ የተጓዘው በኢትዮጵያና በአሜሪካን የሁለትዮሽ የመከላከያ ትብብር ለማጠናከር እንደኾነ፣ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገልጸዋል።
ከፍተኛ የልዑካን ቡድኑ አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የደረሰው ጠዋት እንደኾነም ጠቅሠዋል። አቶ ለማ በመሩት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ውስጥ እነማን እንደተካተቱ አልተገለጸም። (ኢዛ)