በተወሰኑ የአማራና የትግራይ ክልል ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት ተቋርጧል
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ብልሽቱን ለማስተካከል አራት ቀን ይፈጃል
ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 22, 2020)፦ በአማራና በትግራይ ክልሎች የሚገኙ አንዳንድ ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል እንደተቋረጠባቸው ተገለጸ።
የሁለቱ ክልሎች በተወሰኑ ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት የተቋረጠባቸው በአላማጣ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ በደረሰ ብልሽት እንደኾነ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለኢቢሲ ገልጿል።
የኤሌክትሪክ ኃይል ከተቋረጠባቸው ከተሞች መካከል ላሊበላ፣ ሰቆጣ፣ ማይጨውና አላማጣ ይገኙበታል ተብሏል። ብልሽቱን ለማስተካከል አራት ቀን ይፈጃልም ተብሏል። (ኢዛ)



