በፓርላማ አዲስ አበባ ካላት 23 መቀመጫዎች ብልጽግና ለ22ቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናትና ታዋቂ ሰዎችን በእጩነት አቀረበ

ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ ዶ/ር ይናገር ደሴ፣ ዶ/ር ኢንጂንየር ስለሺ በቀለ፣ ዳግማዊት ሞገስ፣ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ ዛዲግ አብርሃ

ዶ/ር ይናገር ደሴ፣ ዶ/ር ሊያ ታደሰ፣ ዳግማዊት ሞገስ፣ ዶ/ር ኢንጂንየር ስለሺ በቀለ፣ ዛዲግ አብርሃ፣ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ … ይገኙበታል

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 15, 2021)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥን ጨምሮ በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ እያገለገሉ ያሉ ባለሥልጣናት የብልጽግና ፓርቲን በመወከል ለፌዴራል ፓርላማ እንዲወዳደሩ የአዲስ አበባ እጩ ኾነው ምርጫ 2013 ቀረቡ። ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዲስ አበባ 23 መቀመጫዎች ያሏት ሲሆን፤ ብልጽግና 22 እጩዎቹን ማቅረቡ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በእጅ የሚያዝ ገንዘብ መጠን እንዲቀንስ መወሰኑ፤ ኢኮኖሚው ላይ ችግር ይፈጥራል ተብሎ ተሰግቷል

National Bank of Ethiopia

“የአገሪቱ የግብይት ሥርዓት በአብዛኛው በጥሬ ገንዘብ ላይ ተመሥርቶ የሚንቀሳቀስ በመኾኑ፤ በእጅ የሚያዝ ገንዘብ በመቶ እና በሁለት መቶ ሺህ ብር መገደቡ ተጽእኖ ማምጣቱ አይቀርም” ኢኮኖሚስቶች

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 15, 2021)፦ መንግሥት ከባንክ ውጭ በእጅ ሊያዝ የሚችለውን የገንዘብ መጠን ከ1.5 ሚሊዮን ብር ወደ 100 ሺህ እና 200 ሺህ ብር እንዲወርድ ያመጣው መመሪያ አነጋጋሪ ኾኗል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሰሞኑን አሻሻሽሎ ባወጣው መመሪያ መሠረት ከባንክ ውጭ በእጅ መያዝ የሚኖርበት የገንዘብ መጠን በግለሰብ ደረጃ 100 ሺህ ብር፤ በኩባንያ ደረጃ ደግሞ 200 ሺህ ብር ብቻ እንዲኾን አሳውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የአማራ ሕዝብ ምን አደረገ? ምን ፈጸመ? ምን በደለ? ለምን በየቦታው ይገደላል?” የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘው ተሻገር

አቶ አገኘው ተሻገር

በአገረ መንግሥቱ እጣ ፈንታ ላይ መነጋገር ያስፈልጋል ብለዋል

ኢዛ (ቅዳሜ መጋቢት ፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 13, 2021)፦ “የኢትዮጵያ ሕዝብ ሊያዳምጠን ይገባል፤ የአማራ ሕዝብ ምን አደረገ? ምን ፈጸመ? ምን በደለ? ለምን በየቦታው ይገደላል?” ያሉት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አገኘው ተሻገር፤ የሕግ የበላይነት ካልተከበር አገሪቱ ወደሌላ ችግር ልታመራ እንደምትችል ገልጸው፤ በአገረ መንግሥቱ እጣ ፈንታ ላይ መነጋገር እንደሚያሻ አስረድተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመጋቢት 4 ግጥምጥሞሽና አሳሳቢው ኮቪድ 19

የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ የኮሮና ክትባት ሲወስዱ

በቫይረሱ የተጠቃው የመጀመሪያው ሰው በተገኘ ልክ በዓመቱ፤ ክትባቱም መሰጠት ተጀመረ

ኢዛ (ቅዳሜ መጋቢት ፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 13, 2021)፦ ዛሬ መጋቢት 4 ቀን ነው። ልክ የዛሬ ዓመት በወቅቱ አስደንጋጭ የሚባል ዜና የተሰማበት ዕለት ነው። ይህም ዓለምን ሲንጥ በቆየው የኮቪድ 19 ቫይረስ የተያዙ የመጀመሪያው ሰው መገኘቱ ይፋ የደተረገበት ነው። የጤና ሚኒስቴር ኾነው በተሾሙ በቀናው ልዩነት መጋቢት 4 ቀን 2012 ዓ.ም. በቴሌቭዥን ብቅ ብለው በኢትዮጵያ የመጀመሪያው በቫይረሱ የተጠቃ አንድ ሰው መገኘቱን የነገሩን ዶክተር ሊያ ታደሰ ነበሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአሜሪካ መንግሥት ማብራሪያ ኢትዮጵያን አስቆጥቷል

Antony Blinken

የኢትዮጵያ መንግሥት የሚኒስትሩን የአንቶኒ ብሊንከንን ክስ ሐሰተኛ እና መሠረተ ቢስ ውንጀላ ነው ብሎታል

ኢዛ (ቅዳሜ መጋቢት ፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 13, 2021)፦ የአሜሪካ መንግሥት በትግራይ ክልል ጉዳይ እየሰጠ ያለው መግለጫ በተለያዩ መንገዶች ተቃውሞ እየቀረበበትና እውነታውን ያላገናዘበ መኾኑ መገለጽ ከጀመረ ሰነባብቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአማራ ክልል በአዲስ ሰንደቅ ዓላማ ይገለጻል

Amhara Region flag

አማራን አይወክልም የተባለው ባንዲራ እንዲቀየር ተወሰነ

ኢዛ (ቅዳሜ መጋቢት ፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 13, 2021)፦ የአማራ ክልላዊ መንግሥት ሲገለገልበት የነበረውንና የክልሉን ሕዝብ አይገልጽም ተብሎ ሲተች የቆየው የክልሉ ሰንደቅ ዓላማ ለመቀየር የክልሉ ምክር ቤት ውሳኔ አሳለፈ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ እየጨመረ የመጣው የቫይረሱ ተጠቂዎችና የመጀመሪያው ክትባት

የጤና ጥበቃ ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ አስትራዜኒካ የኮሮና ቫይረስ ክትባትን ሲረከቡ

ኢትዮጵያ ሁለት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን የአስትራዜኒካ ክትባት ተረከበች

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 8, 2021)፦ በየዕለቱ በኮቪድ 19 ወረርሽኝ (ኮሮና ቫይረስ) የሚያዙ ሰዎች ቁጥር በቀን እንደገና ከአንድ ሺሕ በላይ እየኾነ መጥቷል። እስከ ዛሬ የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ.ም. ድረስ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር 167,133 ደርሷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ከተሸነፍን ላሸናፊው አቅፈን ሥልጣን በማስረከብ አዲስ ታሪክ እንሠራለን” ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ

PM Abiy Ahmed

“በምርጫው ያሻችሁን ምረጡ፤ ግን ሰላምን አስቀድሙ፤ ያሻችሁን ምረጡ ግን እኩል መድረክ መፈጠሩን አረጋግጡ” ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 8, 2021)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ከሰሞናዊ ንግግራቸው ውስጥ በምርጫ ዙሪያ ያደረጉት አንድ ንግግራቸው ተጠቃሽ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የብሮድካስት ባለሥልጣን ዳይሬክተር ሥራ ለመልቀቅ ጥያቄ ማቅረባቸው ተነገረ

ዶክተር ጌታቸው ድንቁ

ምክንያታቸው ይፋ አልተደረገም

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 8, 2021)፦ ባለፉት ሦስት ዓመታት የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር በመኾን ሲያገለግሉ የቆዩት ዶክተር ጌታቸው ድንቁ ሥራ ለመልቀቅ ጥያቄ ማቅረባቸው እየተነገረ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዘገየው የ40/60 ቤቶች ርክክብ

የ40/60 መኖሪያ ቤቶች

የዘገየው የ40/60 ቤቶች ርክክብ ዘግይቶም ያላለቀ ቤት ይረከባሉ መባሉ አነጋጋሪ ኾኗል

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፳፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. March 8, 2021)፦ የርክክብ ጊዜው የዘገየው የ40/60 ባለእድለኞች ዛሬ ቁልፍ መረከብ መጀመሩ ተገለጸ። ግንባታቸው የዘገየው የ40/60 መኖሪያ ቤቶች በተለያየ ዙር ለባለእድለኞች እጣ የወጣ ቢኾንም ቤቱን መረከብ ሳይችሉ ለዓመታት ቆይተዋል። ይህም ለግንባታው ሙሉ ለሙሉ የከፈሉ የቤት ፈላጊዎችን ሲያማርር መቆየቱ አይዘነጋም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ