ድምፂ ወያኔ ስቱዲዮውም ድምፁም ተይዟል

Dimtsi Weyane

መከላከያና ፌዴራል ፖሊስ ድምፂ ወያኔ ስቱዲዮ ውስጥ ናቸው

ኢዛ (ዓርብ ኅዳር ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. December 4, 2020)፦ የሕወሓት ቡድን ዋነኛ የፕሮፓጋንዳ ማሰራጫ ጣቢያ በመኾን የሚታወቀው የድምፂ ወያኔ ስቱዲዮ ዛሬ ዓርብ ኅዳር 25 ቀን 2013 ዓ.ም. በአገር መከላከያ እና የፌዴራል ፖሊስ ተቆጣጥሮታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፖለቲከኛና ደራሲ አንዳርጋቸው ጽጌ ለመከላከያ የመቶ ሺህ ብር ቼክ ድጋፍ ሰጡ

ፖለቲከኛ እና ደራሲ አንዳርጋቸው ጽጌ የመቶ ሺህ ብር ቼክ ለመከላከያ ውጭ ግንኙነት ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል ቡልቲ ሲያስረክቡ

ሕወሓት በአገር መከላከያ ሠራዊቱ ላይ በተኛበት የፈጸመውን እጅግ አስከፊና አሳዛኝ ጥቃት አውግዘዋል

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፳፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. December 3, 2020)፦ ራሳቸውን ከፖለቲካ ፓርቲ አባልነት ያገለሉት ፖለቲከኛ እና ደራሲ አንዳርጋቸው ጽጌ፤ ከአዲሱ መጽሐፋቸው ሽያጭ ገቢ ካገኙት ላይ የአንድ መቶ ሺህ ብር ቼክ ለመከላከያ ሚኒስቴር አበረከቱ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ተጠባቂው የብልጽግና ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ነገ ይጀመራል

Prosperity Party

አጀንዳው ወቅታዊ አገራዊ ጉዳይ ነው

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፳፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. December 3, 2020)፦ በተለያዩ ወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ አቅጣጫ ያስቀምጣል ተብሎ የሚጠበቀው የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ነገ ዓርብ ኅዳር 25 ቀን ዓ.ም. ይጀምራል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምርጫ ዙሪያ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር መከሩ

PM Abiy Ahmed held a meeting with Opposition parties and Civic organizations

ምርጫው ዴሞክራሲያዊ እንዲኾን መግባባት ላይ መደረሱ ተገለጸ
የተፎካካሪ ፓርቲዎች ጠቅላይ ሚኒስትሩን አመስግነዋል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፳፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. December 2, 2020)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች አመራሮች እና የሲቪክ ማኅበራት ተወካዮች ጋር በቀጣዩ ምርጫ ዙሪያ መወያየታቸውንና ምርጫው ዴሞክራሲያዊ የሚኾንበትን መንገድ በተመለከተ መግባባት ላይ ስለመደረሱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ፍርድ ቤት ቀረበ

Journalist Dawit Kebede, Awramba Times

ለፖሊስ የ13 ቀን የምርመራ ጊዜ ተሰጠው

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፳፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. December 2, 2020)፦ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ የተዛባ መረጃ በማውጣትና ግጭት በመቀስቀስ፣ ሕገ መንግሥቱንና ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመናድ ሲንቀሳቀስ እንደነበርና ከዚሁ ጋር በተያያዘ ወንጀል ተጠርጥሮ ዛሬ ረቡዕ ኅዳር 23 ቀን 2013 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀረበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በመቀሌ ከተማ በመንግሥት የማይታወቅ የጦር መሣሪያ ዴፖ ተገኘ

በመቀሌ የተገኘውና መከላከያና ሰሜን ዕዝ የማያውቁት የጦር መሣሪያ ማከማቻ ዴፖ

በመቀሌ ቤት ለቤት ፍተሻ ተጀምሯል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፳፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. December 2, 2020)፦ በመቀሌ ከተማ ውስጥ በመንግሥትም ኾነ በሰሜን ዕዝ የማይታወቅና የጁንታው የሕወሓት ቡድን ለጥፋት ሊጠቀምበት የነበረ የጦር መሣሪያ ማከማቻ ዴፖ መገኘቱንና በአገር መከላከያ እጅ መግባቱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፌዴራል ፖሊስ ልዩ ኮማንዶና የወንጀል ምርመራ ቡድን መቀሌ ገባ

TPLF

ቡድኑ ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በመኾን ወንጀለኞችን ማደን ጀምሯል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፳፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. December 2, 2020)፦ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ማምሻውን እንዳስታወቀው የኮሚሽኑ ልዩ የኮማንዶና የወንጀል ምርመራ ቡድን ዛሬ መቀሌ ገብቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በትግራይ አንዳንድ ከተሞች ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎት መስጠት ጀመረ

Ethio Telecom

በአላማጣ ሙሉ ለሙሉ፣ በዳንሻ፣ ተርካን፣ ሑመራ፣ ሽራሮ፣ ማይጸብሪ እና ማይካድራ በከፊል አገልግሎት መስጠት ጀምሯል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፳፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. December 2, 2020)፦ ኢትዮ ቴሌኮምም በትግራይ ክልል የቴሌኮም አገልግሎትን ለማስጀመር እየሠራ መኾኑን አስታውቆ፤ በአሁኑ ወቅትም በአላማጣ ከተማ ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት ጀምሯል። በሌሎች የክልሉ አካባቢዎችም በከፊል አገልግሎት ስለመጀመሩ ያስታወቀው ኢትዮ ቴሌኮም፤ በከፊል አገልግሎት ከተጀመረባቸው ከተሞች ውስጥ ዳንሻ፣ ተርካን፣ ሑመራ፣ ሽራሮ፣ ማይጸብሪ እና ማይካድራ ይገኙበታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በትግራይ ክልል የተከፈቱ የባንክ አካውንቶች እንዲንቀሳቀሱ ተፈቀደ

National Bank of Ethiopia

በክልሉ የሚገኙ ከ600 በላይ የባንክ ቅርንጫፎች የሚከፈቱበት ሁኔታ እየታየ ነው

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፳፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. December 2, 2020)፦ በትግራይ ክልል ውስጥ በሚገኙ የባንክ ቅርንጫፎች አካውንት ከፍተው፤ ከትግራይ ክልል ውጭ አካውንታቸውን ማንቀሳቀስ እንዳይችሉ ተጥሎ የነበረው እገዳ ተነስቶ፤ በየትኛውም የአገሪቱ ክፍል አካውንታቸውን እንዲያንቀሳቅሱ ተፈቀደ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቀድሞው ሚኒስትርና የብአዴን ከፍተኛ አመራር ከአገር እንዳይወጡ ተከለከሉ

Kebede Chane

ለሕወሓት ጁንታ ቡድን ምስጢር በማቀበል ተጠርጥረው ስለመኾኑ እየተነገረ ነው

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. December 1, 2020)፦ ከቀድሞ የብአዴን ከፍተኛ አመራሮች መካከል አንዱ የኾኑትና በተለያዩ የመንግሥት የኃላፊነት ቦታዎች ላይ በመመደብ እስካሁን ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ ከበደ ጫኔ ከአገር ለመውጣት ያደረጉት ሙከራ በጸጥታ ኃይሎች ተገታ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ