S3457 እና HR2003 በተመለከተ (ከአማኑኤል ዘሰላም)
S3457 እና HR2003 በተመለከተ - መስተዋል ያለበት የጋራ የዲፕሎማሲ ሥራ
ከአማኑኤል ዘሰላም This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.
በቅድሚያ በሀገር ቤትና ከሀገር ውጭ ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ሁሉ እንኳና ለአዲሱ ዓመት በሠላምና በጤና እግዚአብሔር አደረሳችሁ! አደረሰን! እላለሁ። «መጪው ዓመትም በታሪካችን አዲስ ምዕራፍ የሚጀመረበትና በአዲስ አመለካከት በጋራ ሀገራችን ኢትዮጵያ ካለችበት የድህነት አዘቅት ውስጥ የምናወጣበት ዓመት ያድርግልን!» እያልኩ ለአንባብያን ለማካፈል የፈለኳቸውንና ከውጭ ግንኙነት እና የዲፕሎማሲ ሥራ ጋራ የተገናኙ አንዳንድ ሃሳቦችን በትህትና ለማቅረብ እሞክራለሁ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...

በ1930ዎቹ የኢጣልያ አገዛዝ ሊያበቃ ሲል፣ ክፉ ረሃብ በአዲስ አበባ ውስጥ እንደነበረ አስታውሳለሁ፤ ምናልባትም በገጠር የከፋና ወደ ችጋር የሚጠጋ ሳይሆን አልቀረም የሚል ግምት አለኝ፤ በአፄ ኃይለሥላሴ አገዛዝ ችጋርን በዓይኔ ያየሁበትና ቀምሼው ምንነቱን ያወቅሁበት ነበር። በዚህም ምክንያት ብዙ ተናግሬአለሁ፣ ብዙም ጽፌአለሁ።
የጀመርነው ሃሳብን በነፃነት መግለጽ መቻል፣ መከባበር፣ እውቀትን ከፍ ከፍ ማድረግ ሊበረታታ ይገባል። አንዳችን የሌላኛችንን ሃሳብ ማክበር ስንችል እኛነታችንን ሳይሆን ሃሳባችንን እያብጠለጠልነውና እያብላላነው መሄድ ስንችል በአስመራ መንገድ ይሁን በቸርችል ጎዳና ብቻ ቤተመንግሥት ከች ማለታችን አይቀርም። ሁላችንም የምንተጋው ነፃነታችንን እንድናገኝ ነው። ባርነትን ለመምረጥ እሰጥ አገባው ባላስፈለገንም ነበር። 


