ጳጳሶችና ስደት

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

እንዲያውም ርእሱን ካህናትና ስደት ብለው ይሻላል፤ ካህናት የሁሉንም ሃይማኖቶች መሪዎችን ይመለከታል፤ ዓላማዬም ሁሉም የኃይማኖት መሪዎችን የሚነካ ነው፤ ነገር ግን የእኔ እውቀት በክርስትናው ላይ ጎላ ያለ በመሆኑ የክርስቲያኖቹ መሪዎች ላይ ያተኮርኩ ቢመስልም ሁሉንም ይመለከታል፤ በተለይ መነኩሴዎች ላይ የማነጣጥርበትም የተለየ ምክንያት አለኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የምንበቃው፣ በአለት ላይ የቆመ ፓርቲ ሲኖረን ነው

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ይገረም አለሙ

አቶ ግርማ ሠይፉ ማሩ / Girma Seifu Maru

ከ2002 ዓ.ም. እስከ እስከ 2007 ዓ.ም. ድረስ የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ ግርማ ሰይፉ "ለዴሞክራሲ ሥርዓት ምን ዓይነት ፓርቲ ያስፈልገናል?" በሚል ርዕስ ያቀረቡትን ጽሁፍ ለማንበብ የጓጓሁት የአንድነት ም/ሊቀመንበር ነበሩና ከተግባር ተሞክሮአቸው በመነሳት ድክመት ጥንካሬን መለስ ብለው ቃኝተው መሆን ያለበትን ያመላክታሉ በሚል ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለዴሞክራሲ ሥርዓት ምን ዓይነት ፓርቲ ያስፈልገናል?

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ (በግራ) ዶ/ር መረራ ጉዲና (በቀኝ) / Prof. Beyene Petros (Left) & Dr. Merera Gudina (Right). (AP Photo/Mulugeta Ayene)ግርማ ሠይፉ ማሩ

በሀገራችን የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበራት እንዲሁም የሚዲያ ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ እንደሆነ ሁሉም ይረዳዋል ማለት ባይቻልም፤ በተለይ የፖለቲካ ፓርቲ አባል አመራር የሆኑ ሰዎች ይጠፋቸዋል ብሎ የሚገምት ላይኖር ይችላል። እውነቱ ግን ከዚህ የተለየ ነው። በአሁኑ ጊዜ የፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ ሰዎች የሚሳተፉት በዋነኝነት በሀገራችን የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን መዋጮ በማስላት ሳይሆን፤ ገዢውን ፓርቲ በማስወገድ ላይ ብቻ ያጠነጠነ ይመስላል። ይህንንም ማድረግ የሚፈልጉት ደግሞ በትርፍ ጊዜያቸው ከሥራ መልስ ወይም በጡረታ ጊዚያቸው ነው። ይህን ሲያደርጉ ደግሞ የብዙ ወጣቶች ጊዜና ጉልበት መስመር ባልያዘ አቅጣጫ እንደሚመሩ አይረዱም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአፍሪካ ቀንድ ተስፋ ሊኖረው ይችላልን?

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

የአፍሪካ ቀንድ ተስፋ ሊኖረው ይችላልን? Horn of Africaፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ)

እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2014 “ለአፍሪካ ተስፋ ሊኖረው ይችላልን?“ በሚል ርዕስ አንድ ትችት ጽፌ ነበር። ያንን ትችት የጻፍኩት ባለፉት ጥቂት አስርት ዓመታት ውስጥ ተንሰራፍቶ በሚገኘው እና ማቆሚያ በሌለው በአፍሪካ ሰው ሰራሽ ቀውስ ምክንያት ምንም ዓይነት ተስፋ የሌለኝ በመሆኑ ነበር። እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2014 የመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ (መአሬ) አውዳሚ በሆነ የጎሳ-ኃይማኖት የዘር ማጥፋት ዘመቻ እልቂት ውስጥ ተዘፍቃ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቡ የሻዕቢያ እና የህወሓት እንጂ የህዝብ አይደለም

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ግርማ ካሳ

ሰሞኑን በሰሜኑ የሀገራችን ግዛት ጦርነት ተቀስቅሷል። አስመራም፣ አዲስ አበባም ያሉ ገዢዎች ጦርነት መደረጉን ማመን ብቻ ሳይሆን “ይሄን ደመሰስን፣ ይሄን ያህል ገደልን” እያሉ በመማጸደቅ ላይ ናቸው። ዓለም የትናየት ደርሳለች፣ ትላንናት እኛ እየረዳናቸው ነጻ የወጡ የአፍሪካ ሀገራት እንኳን የትናየት ደርሰዋል፣ እኛ አሁንም መግደልን እንደ ጀብዱ አድርገን እናወራለን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የወያኔ ውድቀት የአደባባይ ምሥጢር መሆኑን የሚያመላክት አጋጣሚ

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ማስተዋል በለጠ (ከአዲስ አበባ)

የወያኔ ውድቀት የአደባባይ ምሥጢር መሆኑን የሚያመላክት አጋጣሚ

ከደቂቃዎች በፊት ከአንዱ የመሥሪያ ቤቴ ቅርንጫፍ ወደ ዋናው መ/ቤት ስመጣ እንዲህ ሆነ። መኪናዋ ውስጥ በተላላኪነት የምትሠራ አንዲት ወጣት፣ ሹፌራችንና እኔ ብቻ ነን የነበርነው። የዛሬው ቀን የከተማችን ወሬ የሆነውን የማትሪክ ፈተና መሰረቅ አነሳሁና የተለጎመውን የሦስታችንንም አንደበት በጋራ የሀገር ጉዳይ ከፈትኩት። በዚህን ዓይነት ሁኔታ እኔ ብዙውን ጊዜ ነገር እለኩስና ዋና ሥራየ ማዳመጥ፣ ማዳነቅና ማውጣጣት ነው። ቀዳሚው ሥራየ ግን የማዋራቸው ሰዎች በኔ ላይ እምነት እንዲኖራቸው ጥረት ማድረግ ነው፤ ሰው ከተጠራጠረህ የልቡን አይናገርም። ዝም ሊል ወይም ሊዋሽህና ሊያታልልህም ይችላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ