ሃይማኖትና አክራሪነት

 

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም

አንድ የአሜሪካ ፈላስፋ የሚተርከው ገጠመኝ አለው፤ አንድ ቀን በእግሩ ሲንሸራሸር ሰዎች አንድ ዛፍ ከብበው ሲጨቃጨቁ ያያል፤ ይጠጋና ሲያዳምጥ ክርክሩ በአንዲት ዛፉ ላይ ባለች የዛፍ አይጥ (የዛፍ አይጥ እኔ ያወጣሁላት ስም ነው፤ በእንግሊዝኛ ስኮረል ትባላለች ረጅም ጭራ ያላት ጸጉራማ ፍራፍሬ ለቃሚ ነች፤) የተነሣ ነው፤ አንዱ ሰው ይቺን የዛፍ አይጥ እዞራታለሁ ይላል፤ ሌላው ደግሞ የለም ዛፉን ትዞራለህ እንጂ አይጥዋን ልትዞራት አትችልም ይላል፤ እዞራታለሁ የሚለው ሰው ለማስረዳት ዛፉን ይዞራል፤ አይጥዋም በዛፉ ላይ ትሽከረከራለች፤ የተሰበሰቡት ሰዎች በዚህ ጉዳይ ለሁለት ተከፍለው ይጨቃጨቃሉ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመለስ ህመም፣ ታክቲክ እና መፃኢ እጣ ፈንታ

ተመስገን ደሳለኝ (ፍትህ ጋዜጣ- አዲስ አበባ)

ሰሞኑን አዲስ አበባ በወሬ መጋኛ ተመታለች። ወሬው በአዲስ አበባ ብቻ የተወሰነ አይደለም። በተለይም በአውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንደ ጉድ እየተራገበ ነው- የ57 ዓመቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በጠና መታመም። ህመማቸውንም ተከትሎ ቤልጂየም ለህክምና መሄዳቸው እና ከፍተኛ ሊባል የሚችል ክብደት የመቀነሳቸውም ወሬ እንዲሁ የመጋኛ ያህል ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

በወቅታዊው በጠ/ይሚ መለስ ጉዳይ ዙሪያ የተደረገ ውይይት (አዲስ)

የመጀመሪያ የህግ ትምህርቱን በህንድ፤ የማስትሬት ዲግሪውን ደግሞ በእንግሊዝ ሀገር የተከታተለው ዳንኤል  ጥላሁን እና በዩኒቨርሲቲ ኦፍ ብሪቲሽ ኮሎምቢያ የህግ ትምህርቱን ተከታትሎ ማስተርሱን በኦታዋ ካናዳ የሰራው ተክለሚካኤል አበበ በቶሮንቶ ካናዳ በሚገኘው የኢሳት ስቱዲዮ በወቅታዊው የጠ/ሚ መለስ ዜናዊ አነጋጋሪ ጉዳይና በሀገሪቱ መጻኢ ጠቅላላ ሁኔታ ከኢትዮጵያ ህገመንግስት አንጻር ሰፊ ውይይት አድርገዋል።

(ሙሉ ውይይቱን ለመከታተል ይህንን ይጫኑ)

ተስፋዬ ገብረአብ ከሚበጀው የሚፈጀው (ዓለማየሁ ገላጋይ)

ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋዬ ገብረአብ ሰሞኑን የኖህን ልጅ ካምን ሆኖ ከረመ ማለት ይቻላል። አባቱ ኖህ በወይን ጠጅ ሰክሮ እራሱን በማይቆጣጠርበት ጊዜ እራቁትነቱን (ነውሩን) ያየውን ካምንአይቶ ያልበቃውን፣ ወንድሞቹም የአባታቸውን እራቁትነት አይተው እንዲሳለቁ የጋበዘውን ካምንይህን በማድረጉም ዘር ማንዘሩ በአባቱ የተረገመውን ካምንተስፋዬ ሆኖ ከረመ። ካምን ለመሆን ህሊና ቢስነት እንጂ ሌላ ችሎታ አለመጠየቁን ተስፋዬ የተረዳው አይመስልም። ድፍረት እንጂ ብልሃት ግድ እንደማይል የገባው አይመስልም። ይህም በሚያቀርባቸው ቁንፅል ታሪኮች ላይ በጉልህ ይነበባል።


ተስፋዬ ገብረአብ ሰሞኑን ካምን የሆነው እንዲህ ነው። ባትወልደውም ያሳደገችውን አገር የታሪክ ጉንፍ እየገላለጠ እራቁትነት ለማየት እጅግ በመጣር ላይ ይገኛል። ለማየት መጣሩ ሳይበቃው ሌሎችም እንዲሳለቁ ‹‹የቅዳሜ ማስታወሻ›› ብሎ በሰየመው ብሎጉ በመጋበዝ ላይ ነው። በተለይ አፄ ምኒልክን፣ አፄ ኃይለሥላሴን፣ እቴጌ ጣይቱ እና እቴጌ መነን የቀጥታ ተጠቂ ለማድረግ ፍላጐት እንዳለው በጉልህ ይታያል። ከእነሱ በሰተጀርባ ደግሞ እኛን ኢላማ አድርጓል፡፡ ‹‹የንጉሠ-ነገሥቱ እናት›› ‹‹የጎጃም ልዕልት›› እና ‹‹የመነን አራተኛ ባል›› በተሰኘ ፅሁፉ እነዚህ አጤዎችና ንግሥቶች ላይ ቦጫቂ የንሥር ጥፍር የመሰለ ብዕሩ ሲያንዣብብ በገሃድ ይስተዋላል።

እንዴት? ለምን? ምን ፍለጋ? ምን ለማትረፍ? ይሄን ከመፈተሻችን በፊት ተስፋዬ ገብረአብን በጥቂቱ ለማየት እንሞክር።


የማይታበለው ነገር ተስፋዬ ገብረአብ ለአማርኛ ሥነ-ፅሁፍ ባለውለታ ነው። ‹‹ያልተመለሰው ባቡር›› ‹‹የቢሾፍቱ ቆሪጦች›› እና ‹‹የቡርቃ ዝምታ›› የተሰኙ ልቦለዶቹ እንደውርዴ ከወላጆቻቸው የወረሱት የዘር ጠባይ ቢኖርባቸውም የትረካ ጥበባቸው ቅርሳችን መሆኑን መካድ አይቻልም። እንዲሁም ሁለት ‹‹ባለቅፅ›› መጽሐፎችንም አበርክቶልናል። ‹‹ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ›› እና ‹‹እፍታ›› የተሰኙት እነዚህ ‹‹ባለቅፅ›› መጽሐፎች ተስፋዬ የጡት አባት ሆኗቸው በጉዲፈቻነት ባያሳድጋቸው ኖሮ ምናልባትም የሥነ- ፅሁፍ አፀድ ውስጥ የማይቀበሩ በጨቅላነት የተቀጠፉ በሆኑ ነበር። ከእነዚህ ሁሉ በኋላ ደግሞ ሁለቱ ‹‹የጋዜጠኛው›› እና ‹‹የደራሲው›› ማስታወሻዎች ተከትለዋል። የዘር በሽታው ካንዱ ሥራ አንዱ የማይሻል ቢሆንም በሁለቱ ‹‹ማስታወሻዎች›› ላይ ተስፋዬ ለጋነቱን አጥቶ፣ እንደዛፍ ተንጋዶ መብቀሉ በጉልህ የሚስተዋልባቸው ሆነዋል።


የተስፋዬ ገብረአብ አብዛኞቹ ሥራዎች (ብሎጉን ጨምሮ) እንደ ገጠር ሴትወይዘሮ መኳኳያቸው ‹‹ጥላሸት›› ነው። ‹‹ጥላሸቱ›› ደግሞ ከስም ማጥፋት ጥቀርሻ የሚገኝ ነው። ይሁንና ሥራዎቹ ገና በፈገግታ ሲቀርቡን ጉራማይሌአቸው የጥላሸት እንዳልሆነ ሁሉ በውበት ይጠልፉናል። ተስፋዬ ‹‹የሚነቅስበት›› የራሱ የሆነ የቋንቋ እሾህም አለው። እየጠቀጠቀ ከሚያደማው ‹‹ድድ›› ሆነ ‹‹አንገት›› ውስጥ ከማዝጐርጐር የሚመነጭ ውበት ያፈልቃል። ይሄንን ደግሞ ተስፋዬ ያውቃልና የስም ማጥፋት ጥቀርሻውን ሆነ መጠቅጠቂያ እሾሁን አይጥልም። ‹‹የጋዜጠኛው ማስታወሻ›› ላይ ስለመኳኳያ ‹‹ጥላሸቱ›› እንዲህ ይላል።
‹‹
በዚህ መጽሐፍ ባልተለመደ ሁኔታ እውነተኛ ስማችሁን ለተጠቀምኩ ሁሉ ባለማስፈቀዴ ይቅርታ እየጠየቅሁ፤ አትቀየሙኝም ብዬ በመገመቴ ደግሞ አመሰግናለሁ።››


ከእጅ ያፈተለከ የጫካ እርግብ ይመስል መጽሐፍን ያህል የረጅም ዘመን ነዋሪ በዘፈቀደ መልቀቅ ከባድ ጥፋት ነው። ተስፋዬ ገብረአብ ሆን ብሎ ለሰራው ጥፋት ይቅርታውን የጥፋቱ አባሪ አድርጐ መልቀቁ ደግሞ ትልቅ ሹፈት ይሆንብናል። ተስፋዬ የጥፋቱን ጥፋትነት ቀድሞ ቢረዳውም እራሱን ገስፆ መተው የሚችል አይመስልም። ምክንያቱ ደግሞ ግልፅ ነው። የተጋባበትን ሳይሆን የለማበትን አንጡራ ባህርይ ስለሚያስተናግድ ብቻ ነው። ልጅ ሆኖ በእናቱ ላይ ያደረገውን ‹‹የደራሲው ማስታወሻ›› ላይ እንዲህ ይተርክልናል። ንዑስ ርዕሱ ‹‹የልጅነት ተራሮች›› ነው።


የጓደኛው የነብዩ አባት ኢሬቻን ለማክበር ወደሆራ እየወሰዱአቸው ነው። መንገድ ላይ ስለክብረ በዓሉ መልካም መልካም ነገር ይነግሯቸዋል። ተስፋዬ በጨዋታው መካከል ገብቶ ‹‹እናቴ ግን እንዲህ አልነገረችኝም›› በማለት ክብረ- በዓሉን የሚያጥላላ ነገር ይዘበዝባል። የነብዩ አባት ይሄን በሆዳቸው ይዘው ወደ ተስፋዬ እናት ይሄዳሉ። በነገሩም ላይ ይነጋገራሉ። ሰውዬው ገና እግራቸው ከቤት እንደወጣ እናት ከጉማሬ ቆዳ የተሰራውን አለንጋ አንስተው ተስፋዬ ላይ ይወርዱበታል። ‹‹ስትገርፈኝ እንዲህ እያለች ነበር›› ይላል፡ -


‹‹
የቤትህን ምስጢር ደጅ እያወጣህ ትዘረግፋለህ? ጅላጅል የሆንክ ፍጡር። ለሰው የሚነገርና የማይነገረው መቼ ይሆን የሚገባህ? በችግር ጊዜ ከሚደርሱልኝ፣ ተከባብረን ከኖርነው ጐረቤቶቼ ልታጣላኝ! ጅል! ልጅ የሆንክ ፍጥረት…›› (ከገፅ 38-39)


ተስፋዬ ገብረአብ በመጽሐፎቹና በብሎጉ ሥማቸውን ካነሳቸው አራት ግለሰቦች ጋር በጉዳዩ ላይ አውርቼአለሁ። የእናቱን እሮሮ ነው ሁሉም የደገሙልኝ። በተለይ አንደኛው ‹‹ለምን እኔን ማጥቂያ ያደርገኛል? ስለምን ከሚጐዱኝ ሰዎች ጋር ያያይዘኛል?›› ነበር ያለኝ። ቀላል የሚመስሉ ግን ከባድ የሆኑ የእናቱ ሮሮዎች ተስፋዬ እስካለ ድረስ ለመቀጠላቸው ምንም የሚያጠራጥር ነገር የለበትም። እናቱ ካሉት ውስጥ ‹‹ጅል›› የምትለው ቃል ብቻ የምትታመን አይሆንም። እናት በመሆናቸው የልጃቸውን ጥፋት ከጅልነት ቆጥረውታል፣ ካልሆነም ተስፋዬ ለማደናገሪያነት እናቱ አፍ ላይ ቃሏን አኑሯታል እንጂ ተስፋዬ ጅል አይደለም። ውጤቱን እየገመተ ብቻ ሳይሆን ቀድሞ እያወቀ የሚያደርግ ለመሰሪነት የቀረበ ሰው ነው።


ተስፋዬ ገብረአብ የአካባቢ ተቆርቋሪ ይመስል ከውድቅዳቂ የታሪክ ፌስታል ቆሻሻ ኢትዮጵያዊ ዘንቢል የመስራቱ የሰሞኑ ሙከራ በጅልነት የተፈፀመ አይደለም። ያስወነጨፈብን ጫፉ የክፋት መርዝ የተቀባ የጠላትነት ቀስት ነው። በሚያመረቅዝ የሐፍረት ቁስል ሊመታን ሆን ብሎ የታሪክ ምሁራንን ከለላ አድርጐ ሰንዝሮብናል። ቁንፅል እውነታዎችን በመቅመል መላው ታሪካችንን የውቤ-በረሃ ገድል ሊያስመስለው ሞክሯል። ነገሥታቱን፣ መኳንንቱንና ሴትወይዘሮዎቹን ለድሪያ ብቻ የተፈጠሩ አሻንጉሊቶች በማድረግ ከኢትዮጵያ ውስጥ በታሪክ መኩራትን ጠራርጐ ለማጥፋት አልሞ አንዲት የዶሎዶመች ሙሬ አዘጋጅቷል።


ኢትዮጵያዊ የስብዕና ነውጥ በመሻት ከታሪክ ነቁጥ ተነስቶ የፃፈው አንዱ ሥራው ‹‹የንጉሠ ነገሥቱ እናት›› የሚል ርዕስ ተሰጥቶታል፡፡ የሚተርከው አጤ ምኒልክ ‹‹ከሥራየ ቤት›› (ገረድ) ስለወለዷት ሸዋረጋ ነው። ገና በእናቷ ሆድ ሳለች ከአጤ ምኒልክ እንደተረገዘች ያወቁት እቴጌ ጣይቱ ከቤተመንግሥት እንዳባረሯት ይተርካል። የሰባት አመት ልጅ ሳለች እናቷ ስለሞተችባት እንዴት የመከራ ጊዜ እንደገፋች ያጫውተናል። በመጨረሻ ወታደር አግብታ ሐረር ስትኖር የአባቷ ስም ማተቧ ላይ ተፅፎ በመገኘቱ ባሏ ወደቤተመንግሥት ያመጣታል። አጤ ምኒልክ ከልጃገረዶች መካከል ይለይዋታል፣ ለራስ አሊም ይድሯታል። 1888 .. ልጅ እያሱ የተወለደው ከሸዋረጋ እንደሆነ ይነግረናል።


እዚህ የተስፋዬ ትርክት ውስጥ ፅሁፉን ወደ ውሸትነት ሊለውጥ የሚችል ከፍተኛ የዘመን ዝንፈት ይታያል። ሸዋረጋ ስትረገዝ እናቷን ከቤተመንግሥት ያባረሯት እቴጌ ጣይቱ እንደሆኑ በገደምዳሜ ተነግሮናል። እንዲያ ከሆነ ጉዳዩ የተፈፀመው 1876 .. ወዲህ ነው ማለት ነው። ምክንያቱም እቴጌ ጣይቱና አጤ ምኒልክ ተገናኝተው የተጋቡት በዚህ ዘመን በመሆኑ ነው። ሸዋረጋ እንደው ከአመት በኋላ ተወለደች ቢባል እንኳን 1877 ልጅ ኢያሱን እስከወለደች ጊዜ (1888 .) ያለው ዕድሜ ገና አስራ አንድ ዓመት ብቻ ይሆናል። ተስፋዬ፣ ሸዋረጋ ወታደሩን ያገባችው ለአቅመ ሔዋን ደርሳ መሆኑን ደግሞ ነግሮናል። ታዲያ እንዴት በአስራ አንድ አመት ዕድሜዋ ልትወልድ ቻለች? ድሎት በዝቶ የሴት ወጓን ቀድማ አየች እንዳይባል ሸዋረጋ በችግር ተቆራምዳ ያደገች ናት። ታዲያስ? እንዴት? በምን?...


ሙግት እንጂ ስድብ በመረጃ አይደገፍም። ተስፋዬ ገብረአብ ከዘመኑ አፋትቶና አፍኖ እዚህ ዘመን ያመጣው ታሪክ ለዚህ ትውልድ ነውር የሚመስል ጥቃቅን ነገር ስላለበት ብቻ ሙሉ ትኩረቱን የሰጠው ታሪኩን አቅርቦ አንጡራ ኢትዮጵያውያኑን ማሸማቀቁ ላይ ነው። ከዚያም ኢትዮጵያዊ ኩራትን ሰብሮ ሀገር ተከላካይነትን ማዳከም። ከዚያስ?


ተስፋዬ ገብረአብ ታሪካችንን ከክብሩ አውርዶ የሴትና የወንድ ‹‹ሎሚ ውርወራ›› ብቻ ለማስመሰል የጣረው ተደጋጋሚና አንድ አይነት ቁመና ያላቸውን ታሪክ ነክ ፅሁፎች በማቅረብ ነው። ‹‹የጎጃም ልዕልት›› የተሰኘው ፅሁፉ በንጉሥ ተክለኃይማኖት ልጅ የተነሳው መኳንንታዊ የጋብቻ ውርክብ እንዴት ለአጠቃላይ ጦርነት አስግቶ እንደነበር ይተርክልናል። በመጨረሻ አጤ ምኒልክ እንዴት እንደቋጩት ይነግረናል። ከቁመታቸውም፣ ከወርዳቸውም ቀናንሶ ለመፍጠር የፈለጋቸውን አጤ ምኒሊክ በዘዴ ያስተዋውቀናል።
‹‹
የመነን 4 ባል›› የተሰኘ ፅሁፉ ደግሞ ያነጣጠረው አጼ ኃይለሥላሴ ላይ ነው። መነን በፊት ሁለት አግብተው ፈትተዋል ይለናል።

ልጆችም አሏቸው። በኋላ ሦስተኛ ትዳራቸው ላይ ሳሉ ነው ልጅ ኢያሱ አፋትቶ ለራስ ተፈሪ ሲድራቸው የምንመለከተው ‹‹አምላክ በዚሁ በቃሽ ይበለኝ›› በማለት አራተኛ ትዳራቸውን የተቀበሉት እቴጌ መነን ዘመኑና ዘመነኞቹ ያደረሱባቸው ‹‹ጥቃት›› አጥንታችንን ሰርስሮ ይገባል። ይሄ እንግዲህ ተስፋዬ ገብረአብ ቆንፅሎ እንዳቀረበው ሁሉ ነገሩን ከሁኔታዎች ነጥለን ስንመለከተው ነው ሀፍረት እንዲሰማን የምንሆነው። ከዚያ ውጭ ግን ነገሩ ሌላ ነው። የዚያ ዘመን ፖለቲካዊ ሀይል የሚመነጨው ከዘር ብቻ ነበር። በመሆኑም አካባቢዎችና ግዛቶች ከማዕከላዊ መንግሥት ጋር ተሳስረው የሚቆዩት በፍትሃዊ የበጀት ክፍፍል ሳይሆን በሚዛናዊ የትዳር ስርጭት ነበር። ሁሉም አካባቢና ግዛት የጋብቻ ዝምድናንና መዋለድን ለዙፋኑ የነገ ተስፋ በዋስትናነት ከያዙ ብቻ የሰላሙ ተባባሪዎች ናቸው።

ስለዚህ በንጉሠ ነገሥቱና በመኳንንቱ አካባቢ የነበሩ ሴቶች እንደ ዋነኛ የፖለቲካ መሣሪያ መታየታቸው ግድ ነበር ይሄ በእኛ ብቻ ሳይሆን በአውሮፓውያን ታሪክ ውስጥ ቦታ ያለው ክስተት ነበር። የሔነሪ ስምንተኛን ታሪክ ማንበብ በቂ ነው።


የተስፋዬ ገብረአብ በዚህ ዘመን አስተሳሰብ ለማስዳኘት ከታሪክ ጋር የመካሰስ አዝማሚያ ጅልነት ሳይሆን፣ መሰሪነት እንዳለበት እንድንጠረጥር የሚያደርገን ይሄ ነው። ተስፋዬ ያለጥርጥር ከታሪክ ነቁጥ ኢትዮጵያዊ የስብዕና ነውጥ ለመፍጠር በመሞከር ላይ ነው። በተስፋዬ ገብረአብ መስገር ሁልጊዜም የሚፈልገው ቦታ የሚደርሰው ጀርባውን የተከራየው አካል እንደሆነ ግልፅ ነው። ተስፋዬ የራሱ መዳረሻ የለውም። ተስፋዬን እዚህ ታሪክ የመቅመል ሥራ ውስጥ የከተተው ጀርባን አከራይቶ የመኖር ፈረሳዊ ጣጣ ነው። ጋላቢው መንፈስ በግልፅ እኔ ነኝ ባይልም ከተስፋዬ አሰጋገር አስጋሪውን መለየት የሚያዳግት አይደለም። ግንግን ተስፋዬን ያለጋላቢ የማይሰግር ‹‹የጋማ-ከብት›› አድርጐ አጉልኛ የገራው ማን ይሆን? እሱ እንደሚለው ባንወልደውም አሳድገነዋልና ጀርባን አከራይቶ የመኖር ፖለቲካዊ ስብዕናው የእኛም መሰደቢያ ገመና ሳይሆን ይቀራል? ‹‹አሳዳጊ…›› በሚል የገመና ተጋሪዎቹ መሆናችን እርግጥ ነው፡፡

 

ፍትህ ሳምንታዊ ጋዜጣ (አዲስ አባባ)

‹‹ይቅርታ›› የኢህአዴግ ቃጭል? ወይስ…

በተመስገን ደሳለኝ (ፍትህ ጋዜጣ - አዲስ አበባ)

አዲስ አበባ በለውጥ ፍላጐት ከአፍ እስከ ገደቧ ታጥናለች። እዚህም እዚያም የፖለቲካ ወግ ይጠሰቃል። በቡድን ሆነው፣ በስሜት ተውጠው በፖለቲካ ጉዳይ የሚከራከሩ በርክትዋል፡ ፡ ለዓመታት የፖለቲካ ጉዳይ ‹‹ፆም›› የሆነባቸው የመንግስት መስሪያ ቤቶች ሳይቀሩ ጎራ ለይተው በሚከራከሩ ሠራተኞቻቸው ተፈስገዋል፡፡ ‹‹ቅንጅቱ መንግሥት ለመመስረት የሚያስችል ድምፅ አግኝቷል›› ይላል አንዱ። ‹‹ቢሆንም ኢህአዴግ ይገግማል!›› ሲል ይመልሳል፤ ኢህአዴግ በምርጫ ስልጣን አይለቅም የሚል አቋም ያለው ተከራካሪ፡፡ ሙሉውን አስነብበኝ ...

ያስፈራል፤ ግን ኢትዮጵያ አትፈርስም!

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

ይቺ ኢትዮጵያ የምትባል አገር ስንት የመከራ ወንዞችን ተሻግራለች! ገና ስንት ትሻገራለች! ስንት የግፍ ተራራዎችን አቋርጣለች! ገና ስንት ታቋርጣለች! ስንት የበደል ሰይፎችንና ጦሮችን አምክናለች! ገና ስንት ታመክናለች! ስንት የውጭ ኃይሎችን አሳፍራለች! ገና ስንቱን ታሳፍራለች! ስንት አምባገ- ነኖችን እያለቀሰች ቀብራለች! ገና ስንቱን ትቀብራለች! ጭቆና ከኢትዮጵያውያን ደም ሙልጭ ብሎ ወጥቶ በነፃነት፣ በእኩልነት፣ በዳኝነት በጠራ ደም እስቲተካ ድረስ ኢትዮጵያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ዘርግታ ትጸልያለች! እግዚአብሔርም ቃል ኪዳን አለበት ይሰማታል! የኃያላን ኃያል ኢትዮጵያ እንድትፈርስ አይፈቅድም! ሙሉውን አስነብበኝ ...

"በእነ እስክንድር ነጋ ችሎት የተሰየሙት ዳኛ የእውቀት ችግር የለባቸውም" ከፍተኛ የህግ ባለሙያ

በታምሩ ገዳ

እውቁ የነጻ ፕሬስ አባል፡ ጋዜጠኛ እና ጸሃፊ እስክንድር ነጋ እና የአንድነት ፓርቲው ከፍተኛ አመራር አቶ አንዱአለም አራጌን ጨምሮ ሃያ አራት ጋዜጠኞች ፡የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት እና የሰብአዊ መብት ተሟጓቾች በኢህአዴግ መራሹ ፍርድ ቤት ከአስር ወራት በላይ መመላለስ በሁዋሏ ሰሞኑን "ፋተኛ ናችሁ" የሚል ውሳኔ ማሰተላለፉ ይታወቃል፡፡ ተከሳሾች የተጠቀሰባቸው የህግ አንቀጽ በቅርቡ ረቅቆ የጸደቀው የጸረ አሸባሪነት እና የተሻሻለው የፕሬስ ህግ መሆኑን የተገነዘቡ በረካታ እለማቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በውሳኔው በእጅጉ ያዘኑ እና የአገሪቱ የዲሞክራሲ እና የሰብአዊ መብት አያያያዝ በብርቱ እንዳሳሰባቸው በመግለጽ ለገዤው የኢህዴግ መንግስት ባለስልጣናት ወሳኔው እንዲያስቀይሩ ተማጽኖአቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው፡፡ የሁኔታውን ወቅታዊነት እና አስሳቢነት በተመለከት በምድረ አሜሪካ ከላስ ቭጋስ ከተማ የሚሰራጨው የህብር ራዲዮ በአዲስ አበባ የሚኖሩ እና በህግ እና ተዛማጅ ስራዎች የሚተዳደሩ አንድ ታዋቂ የህግ ባለሙያ አነጋግሯል፡፡ እኝህ ባለሙያ በወቅቱ በአገሪቱ ውስጥ ካላው ሃሳብን በነጻ የመግለጽ መብት ጋር በተያያዝ በዜጎች ላይ የሚደረጉትን ማስፈራራት ፡ ወከባዋች እና እስራትን ከግንዛቤ ውስጥ በመክተት ሰማቸው እንዳይጠቀስ በቅድሚያ ጠይቀዋል፡፡ የዝግጅት ክፍሉም ጥያቄያችውን በማክበር "አቶ አወቀ" በሚል የብእር ስም በመጠቀም የራዲዮው የምእራብ አውሮፓ ልዩ ዘጋቢ ታምሩ ገዳ ቃለምልልሱን አንደሚከተለው አቅርቦታል፡፡ መልካም ንባብ ይሁንሎት ፡፡


ጥያቄ፡- እርሶ በኢትዮጵያ ውስጥ ሰለነበሩት ሆነ አሁን ስላሉት በጣት ስለሚቆጠሩት የፕሬስ ውጤቶች ምን ያህል ቅርበትነት አሎት?


አቶ አወቀ ፡- "በተለያዩ አጋጣሚዎች እና ከስራዩ ጋር ተዛማጅንት ባላቸው መለኩ ከምርጫ 97 አ.ም በፊት ሆነ በሁዋላ እብዛኞቹን የነጻ ፕሬስ ውጤቶችን እከታተል ነበር፡፡ "
ጥያቄ፡- ታዲያ የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ተከታታይ ጽሁፎችን የማንበቡ እድል ነበሮት ?


አቶ አወቀ፡-"ምርጫውን ተከትሎ አብዛኞቹ ጋዜጠኞች ታስረው፡ ገሚሶቹ ደርጅቶቻቸው በመንግስት ሃይሎች ከተዘጉባቸው እና ከተሰደዱ በሁዋላ በተለያዩ ድህረ ገጾች እማካኝነት የሚወጡት ጽሁፎችን እከታተላለሁ ፡፡ከእነርሱ መካከል የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የተለያዩ ወቅታዊ ጸሁፎችን አነብ ነበር፡፡"


ጥያቄ፡- ታዲያ ለእሰክንድር ጽሁፎች እንግዳ ካልሆኑ እውን ገዤው መንግስት እንደሚለው የእስክንድር ጽሁፎች ይህንን ያህል የመንግስት የስልጣን ህልውናን የሚፈታተኑ : ህዝብ በህዝብ ላይ ወይም ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲነሳ የሚቀሰቅሱ ነበሩ?


አቶ አወቀ ፡- "በጭራሽ፡፡ እኔ እስከሚገባኝ እና የጽሁፎቹን መንፈስ በቅንነት ለተመለከተው ለመንግስት ተብዩው ሆነ ለሰርአቱ አፈቀላጤዎች የማነቃቂያ ደውሎች አና አሰተማሪዎች እንጂ በተቃራኒው ወይም በአፍራሽነት የሚታዩ አልነበሩም ፡፡ጽሁፎቹን ባትወዳቸው እንኳን በሰለጠነው አለም ሁልጊዜ እንደሚደረገው ለጽሁፎቹ ተቃራኒ ወይም የመንግስትን አቋም የሚያንጸባርቁ ምላሾችን መሰጠት ይቻላል፡፡ ለእነደዚህ አይነቱ ምላሾች የመንግስት ሰዎች የሚቦዝኑ አይመሰለኝም ፡፡ ወይም ጽሁፎቹን አንብበህ ታዲያ ምንድነው ይደርግ የሚለው ?( so what?) በማለት ጽሁፉቹን በነጻ አመለካከት ደረጃ ፈር ህ የመታልፋቸው እንጂ አንደዚህ እስኪ የዋጣልን ምን ታመጣለህ ብለህ ጥርስ የምትነክስባቸው አየመስሉኝም፡፡"
ጥያቄ፡- የእስክንድር ጽሁፎች ሆኑ አሰተያየቶቹ የመንግስትን ህልውና አያናጉም ካሉኝ ገዤው መንግሰት የህንን ሁሉ ወራት እና የህዝብ ገንዘብ እያባከነ ለምን በእነ እሰክንድር ላይ የቅጣት በትሩን ለመሰንዘር የፈለገ ይምሰሎታል?


አቶ አወቀ ፡- "እስከ ዛሬ ድረስ ለፕሬሱ እና ለፍርድ ቤቶች ካለኝ ቀረቤታ አኳያ በህትመት ሆነ በኤሌክትሮኔክስ መልክ የሚሰራጩ የፕሬስ ውጤቶች ህዝቡን ቀስቅሰው በመንግስት ላይ አመጻ ያስነሱበት ወይም ህዝቡ እርስ በርሱ ደም እንዲቃባ ምክንያት የሆኑበት አጋጣሚን አላስታውስም፡፡እነ እስክነድርን በተመለከት በአጠቃላይ የተጠቀሱባቸው የህግ እንቀጾችን ስመለከታቸው ከበድ ያለ የቅጣት ብይን የሚያሰበይኑባቸው በመሆናቸው በተከሳሾቹ ላያ የስነልቦና እና የሞራል ኪሳራ ለመፍጠር፡ተከሳሾቹን ለማሸማቀቅ እና ከዛሬ ነገ ምን እንሆን ይሆን በሚል ስጋት ተጠምደው ሁለተኛ ፊታቸውን ወደ ቆሙለት ሃሳብን በነጻ የመግለጽ እና የዲሞክራሲ መብት ተጠቃሚዎች እንዳይሆኑ ለማድርግ የተወጠነ የፓለቲካ እቅድ ይመስለኛል፡፡"

 


ጥያቄ፡-የህዝቡን አመለካከት እንዴት ይመለከቱታል?


አቶ አወቀ ፡- "ሁኔታው በአብዛኛው ህዝብ ዘንድ ከፍተኛ የፍርሃት ድባብ ያጠላ የመስላል፡፡ ሁሉም ሰው ምን እየተደረገ እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል፡፡ የመንግስት የመገናኛ ብዙሃናት እና ባለሰልጣናቱ ውሸታሞች እንደሆኑ ህዝቡ ያውቃል፡፡እንዴ ፍርድ ቤቱ በተከሳቹ ላይ የፍርድ ውሳኔ ከማሳለፉ በፊት በመንግስት መገናኛ ብዙሃናት አማካኝነት በተከሳሾቹ ላይ የተከፈቱት የተለያዩ የስም ማጥፋት ዘመቻዎች ምን አይነት መልእክትን ለማሰተላለፍ እንደተፈለገ እና የፍርድ ቤቱ ውሳኔም ቢሆን ምን እንደሚሆን ቀድሞውንም ማወቅ አይከብድም ፡፡ ሌላው ቀረቶ ምን አልባት አንተም ቢሆን ታዝበህ ከሆነ የአገዛዙ ባለስልጣናት እስከአሁን ድረስ ሊዘጉት ወይም ሊያስተጓጉሉት ያልቻሉት እና በርካታ ወጣቶችን የሚያሳትፈው የወዳጆች መገናኛ ድህረ ገጽ የሆነው ፌስ ቡክ (Face Book) ላይ አገዛዙን የሚተቹ ጽሁፎች ሲወጡ ብዙ ሰዎች ጽሁፉን በተመለከተ የራሳቸው የሆነ የድጋፍ ይሁን የተቃውሞ አሰተያየትን ከመሰጠት ቢቻላቸው ጽሁፉን አንብበው ካጣጣሙ በሁዋላ ዝምታን አሊያም ጽሁፉን ወድጄዋለሁ( I like it ) የምትለውን ሳጥን መንካት ብቻ ይመረጣሉ ፡፡ጽሁፉ ፖለቲካዊ ይዘት ከሌለው ደግሞ የተላያዩ የአሰተያየት አይነቶችን ሲያዥጎደጉዱ ታያለህ ፡፡ይህ ሁሉ እንግዲህ የሚያሳየው ከባድ የፍርሃት ደመና በህዝቡ ላይ ማንጃበቡን እንጂ የፌስ ቡክ አላማን እና ሚናውን ያለማወቅ አይመሰለኝም፡፡ የሚገርምህ ነገር የመንግስት ሰራተኞች ሳይቀሩ ወደ ቢሯቸው ከመግባታቸው ቀድመው አርብ ጠዋት ገበያ ላይ የሚውለውን ፍትህ የተባለውን ነጻ ጋዜጣን ለመግዛት ሲሻሙ ታያለህ ፡፡ ነገር ግን ሁሉም በጽሁፉ ዙሪያ በእረፍት ሰአታቸው ከመወያየት ስሜታቸውን በጉያቸው ውስጥ ደብቀው ከስራ መልስ ወደቤታቸው ሲሄዱ የምታየው ፡፡ "


ጥያቄ፡-ፍርድ ቤቱ በእነ እስክንድር ጉዳይ ላይ ምን ያህል አመት ይፈረድባቸዋል ብለው የገምታሉ?


አቶ አወቀ ፡- " በእኔ አመለካከት ቁምነገሩ ስንት አመት ይፈርድባቸዋል ወይም ምን ያደረጋቸዋል የሚለው ጉዳይ ሳይሆን ከመ መሪያው አንስቶ ተከሳሾቹ መከሰሳቸው ተገቢ ነበር? ወይስ አይደለም? የሚለው ጥያቄ መመለስ ነበረበት ፡፡ይህንን ምላሽ ስናገኝ ፍርዱ ምን ይሆናል የሚለውን ጥያቄ መመለስ ከባድ አይሆንም፡፡"


ጥያቄ፡-በህገ መንገስቱ መሰረት ፍ/ ቤቶች ከፖለቲካ ተጸእኖ ነጻ እንደሆኑ ነው የሚነገረው ፡፡ታዲያ የእነ እስክነድር ነጋን ጉዳይን የተመለከተው ችሎት ነጻ ነበር ማለት አይቻልም?
አቶ አወቀ ፡- "ወዳጄ እንዴት እንደዚያ ብልህ ታስባለህ? "


ጥያቄ፡-እሺ ታዲያ ዳኞቹ የልምድ (የብቃት) ችግር አለባቸው እያሉኝ ነው?


አቶ አወቀ፡-"ችግሩ የልምድ እና የእውቀት ማነስ አይመስለኝም ፡፡ ዋናው ተጠሪነትህ ለማን ነው? የሚለውን ጥያቄ መምለሱ ላይ ነው፡፡ተጠሪነትህ ለእይምሮህ ነው? ፡ለህጉ? ለገዤው መንግስት? ወይስ ለህገመንግስቱ?... ወዘተ?. ለምሳሌ ለህገመንግስቱ ተገዤ ካልሆንክ በመ መሪያው ዙር ትመታለህ ወይም ከችሎት ወንበር ላይ አትቀምጠም፡፡ ለምሳሌ ያህል የእነ እሰክንድር ነጋ የክስ ፋይልን ከሚመለከቱት ከሶስቱ ዳኞች መካከል አንዱ የሆነው ዳኛ ሁሴን ይመር የእውቀት ችግር ያለበት ሰው እንዳልሆነ
ልመሰክርለት አችላላሁ፡፡ የሚያሳዝነው ግን ዳኛ ሁሴን ወደ ችሎት ከመገባቱ በፊት እነ ዳኛ መንበረጸሃይ ታደስ ከአለም ባንክ(World Bank ) እና ከአለማቀፉ የገንዘብ ተቋምInternational Monetary Fund ) በተገኘው ከፍተኛ የገንዘብ እርዳታ ባቋቋሙት "የኢትዮጵያ ዳኞች እና አቃቢያን ህግ ማሰልጠኛ" ተብሎ ከሚጠራው ማእከል ውስጥ በመግባት ሁሉም ዳኞች በእውቀታቸው ሳይሆን ለአገዛዙ ታማኝነታቸውን በተመለከተ ተገምግመው የሚያልፉበት ስርአት በመፈጠሩ አነዚያ ሰልጣኝ የህግ ባለሙያዎች ወደ ተለያዩ ችሎቶች ሲመደቡ ምን ማድረግ እንዳለባቸው ከፖለቲካ ርእዮት አለም ያለተናነስ ትምህርት ሰለሚሰጣቸው በችሎት ወንበር ላይ ሲቀመጡ ወደዱም ጠሉ ይህን መሰሉ ተጽእኖ አለባቸው ፡፡ እንግዲህ እንዚሁ ዳኞች ቢቻላቸው ለፓርቲው ታማኝ መሆን ካልሆነ ግን ስራቸውን ለቅቀው መውጣት አለባቸው ፡፡ ዳኛ ሁሴንም ቢሆን ይህንን የተቋሙን የአመለካከት ማጣሪያ ካለፉ ዳኞች መካከል አንዱ ነው ፡፡ ይህ ደግሞ ከህገ መንግስቱ አነቀጾች ጋር በፈጹም የሚጻረረ አካሄድ ነው ፡፡ቀደም ሲል በነበረው የፍርድ ቤቶች አሰራር ተከሳሾች በየትኛው ዳኛ መዳኘት እንዳለባቸው (በተለይ የፖለቲካ ነክ ተከሳሾች) በየትኛው ዳኛ እና ችሎት መዳኘት እንዳለባቸው በመዝገብ ቤት በኩል እንደ ግዳዩ ክብደት እና ፖለቲካዊ ይዘት ተጣርቶ ነበር የሚመደበው ፡፡ለምሳሌ ያህል ጉዳዩ ጠጣር ከሆነ በእነ ዳኛ መድህን ኬሮስ ችሎት እንደሚሆን ብዙ ሰው ቀደሞ ይገምታል፡፡ግምቱም በአብዛኛው ትክክል ነበር ፡፡በሁዋላ ግን ከላይ የገለጽኩልህ ተቋም ከተከፈተ በሁዋላ ፍርድ ቤትች በሙሉ አንድ ወጥ አሰራር እንዲሰሩ በመደረጉ ( ሁሉም ለገዤው መንግስት ያደሩ በመሆናቸው) መዝገብ ቤቶች ፋይሎችን በማገላበጥ መምደቡን ትተውታል፡፡ ዳኝነት የህሊና ፍርድ መሆኑ እየታወቀ አንዳንድ ጊዜ ዳኞች እንኳን ውስኔ ከማስተላለፋቸው በፊት "መንግስት በውሳኔው ያኮርፍብን ይሆን?" የሚል ስጋት እንዳለባቸው ታዋቂው ደምጻዊ ቴዲ አፍሮ(ቴድሮስ ካሳሁን) "በሰው መግደል" ክስ ቀርቦበት ቸሎቱ ተከሳሹን ጠፋተኛ አድርጎ ከምበየኑ በፊት ዳኞቹ የመንግስትን ( የመነግስት የኮሜኒኬሽን ምክትል ሹም የሆኑት የእነ አቶ ሸመልስ ከማልን አስተያየት) የጠየቀበት ሁኔታን ስትመለከትው ፍርድ ቤቶች ምን ያህል ለስርአቱ ጉዳይ አስፈጻሚዎች መሆናቸውን በቀላሉ ትረዳዋለህ፡፡"


ጥያቄ፡- አሁን ታዲያ ዳኞች በጭራሽ ለህሊናቸው ሲሉ አይፈርዱም እያሉኝ ነው ያሉት?


አቶ አወቀ፡-"ምንም ጥርጥር የለውም ፡፡አንድ ማስረጃ ልጨምርልህ ፡፡ ከሰባት ወራት በፊት ፍርድ ቤቶች ተዘግተው በአዲስ አበባው የጊዮን ሆቴል ውስጥ በእነ አቶ (ጓድ) ሽመልስ ከማል አዘጋጅነት ለሶስት ሳምንታት የዘልቀ በጸረ አሸባሪነት ህጉ እና በፕሬስ አዋጁ ዙሪያ የሙያ ግንዛቤ ማስጨበጫ የሚል ፕሮግራም ተሰጥቶ ነበር ፡፡"
ጥያቄ፡ ታዲያ መንፈሱ "የግንዛቤ ማስጨበጫ" ከሆነ ስህተቱ እምኑ ላይ ነው?


አቶ አወቀ፡-"ችግሩ ሴሚናር መስጠቱ ላይ ሳይሆን ስሚናሩን የሚሰጡት እነማን ናቸው? ተጠሪነታቸውስ ለማን ነው? ከሚለው የህግ ጥያቄ ላይ ማየት ይቻላል፡፡ እነ አቶ ሸመልስ እኮ የፖለቲካ ሹመኞች እና ለአገዛዙ እድሜ መራዘም ቀን ተለሊት የሜሯሯጡ ሰዎች ናቸው ፡፡ እዚህ ላይ አንሱ ለዳኞቹ ይህንን መሰሉን ስልጠና ሲሰጡ "ከዚህ በሁዋላ የምትሰሩት በዚህ መልኩ ነው" ማለታቸውን መዘንጋት የለብንም፡፡ህጉን የመተርጎም ሙሉ ስልጣን የፍርድ ቤቶች መሆኑ እየታወቀ የመንግስት ባለስልጣናት እና አፈቀልጤዎች ዳኞቹን በስበብ አስባቡ ሰብስበው "የእኛ መንፈስ ይህ በመሆኑ እናንተም ወደ ችሎት ስትመለሱ እንዲህ ብላችሁ ተርጉሙልን...ወዘተ" በማለት በፍትህ ስርእቱ ላይ ምን አይነት ጫና እና ግፍ እየፈጸሙ መሆናቸውን ጥንቅቀን ማወቅ ያለብን የመስለኛል፡፡በአጭሩ እነዚህ ዳኞች ከአዳራሹ ሲወጡ እንደ ኮምፒውተር ወይም ሮቦት ሶፍት ዌር (Soft ware programmed) ሆነው ነው የሚወጡት ፡፡ይህ አይነቱ አካሄድ ደግሞ በፍትህ ስርአቱ ላይ እሉታዊ ተጽእኖ እንደሚኖረው በእለት ተእለት ውሳኔዎች ላይ ማየት ይቻላል፡፡"
ጥያቄ ፡- አብዛኞቹ ፍርድ ቤቶች በአሁኑ ወቅት የክስ ፋይሎችን በፍጥነት ውሳኔ እንደሚሰጡ በስፋት ይነገራል....


አቶ አወቀ ፡- "እዚህ ላይ ሰለ የትኞቹ ጉዳዮች እንደምናውራ ጥንቅቀን ማወቅ አለብን ፡፡የፍታብሄር ጉዳይ ነው? ወይስ የደረቅ ወን ል? የእጅ ከፈንጅ? አሊያም የፖለቲካ...? ወዘተ ጉዳይ እያልን መከፋፈል እንችላለን ፡፡ ፍጥነት ስንል ደግሞ ውጤቱ እምኑ ላይ ነው? የሚለውን ማየት አለብን (speeds at the expense of quality)፡፡ በአንድ ወቅት ከእንግሊዝ አገር የህግ ባለሙያዎች በፍርድ ሂደት(Arbitration) ዙሪያ የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ወደ አዲስ አበባ መጡ፡፡ስብሰባውን ይመሩት የነበሩት ፕ/ቱ አቶ ውብሸት ሺፈራው ነበሩ ፡፡ ነጮቹም "ፋይሎችን በስንት ጊዜያት እንደሚጠናቀቁ" ለአቶ ውብሸት ጥያቄ ቢጤ ወረወሩላቸው፡፡ ዳኛ አቶ ውብሸትም "በስድስት ወራት ውስጥ እናጠናቅቃለን" አሉ ፡፡ በአዳራሹ ውስጥ የነበሩት ተሳታፊዎች በሙሉ ሳቅ በሳቅ ሆኑ፡፡ ፈረንጆቹም የአቶ ውብሸት ምላሽን ተከትሎ በታሳታፊዎቹ ላይ ይነበብ የነበረው ከቁጥጥር ውጭ የሆነው ሳቅ ምስጢር ገብቷቸው አነርሱም በመገረም ተሳሳቁ ፡፡ ነጮቹ የመልሶቹ ይዘት ሰለገባችው ከዚያ በሁዋላ ጥያቄ አላነሱም ፡፡"


ጥያቄ ፡- አነ እስክንድር ነጋ "ጠፋተኛ ናችሁ" ከተባሉ በሁዋላ ውሳኔውን በተመለከተ የሚሰጡት አስተያየት ካለ ብሎ ችሎቱ መጠየቅ ሲገባው ችሎቱ ለእነሩሱ (ለተከሳሾቹ ) ይህንን መብታቸውን መንፈጉን ከህግ አኳያ እንዴት ይመለከቱታል?


አቶ አወቀ ፡-"የፍ/ ቤቱን ምስል ከላይ ለመግለጽ ሞክሬ ነበር እኮ ፡፡በአገሪቱ ከ1960ዎቹ እ.ኤ.አ  ምሮ ሲስራበት የነበረው እና አለማቀፋዊ ይዘት ያለው የወን ለኛ መቅጫ ስነስርአት ህግ አንቀጽ 148 እና 149 በአጭሩ ብገልጽልህ አቃቤ ህግ ሆነ ተከሳሾች ወይም የተከሳቹ ጠበቆች ውሳኔውን በተመለከት አስተያየት የመስጠት እኩል መብት እንዳላቸው፡በተለይ ተከሳሾች ከሁለት በላይ ከሆኑ ሰብሳቢው ዳኛ ማንኛው ተከሳሽ ቀደሞ መናገር እንዳለበት በመምረጥ የመጨረሻውን አስተያየት ተከሳሹ ወይም ጠበቃው እንደሚያደረጉ በህጉ ላይ ቁልጭ ብሎ ተቀምጦ ሳለ አቃቤ ህግ ይህንን መብት ተሰጥቶት አነ እሰክንድር ነጋ በስተመጨረሻ የህጉ ሰለባ እና ተጠቂዎች እንደሚሆኑ እየታወቀ፡ፍርድ ቤቱ "ጥፋተኛ ናቸው" ባላቸው የክስ ፋይል ከትንሹ ቅጣት አንስቶ እስከ ከፍተኛው የፍርድ ጣሪያ ሊፍረድባቸው አንደሚችል አየታወቀ "አሰተያየት አተሰጡም" ማለቱ ፊውዳል እና በዝባዥ በተባለው በአጼ ሃይለስላሴ ዘመን ንጉሱን ሊገለብጡ ከወንድማቸው ከግርማሜ ጋር በ1953 አ/ም "አሲረዋል" ተብለው የስቅላት ቅጣት የተበየነባቸው መንግስቱ ነዋይ እንኳን በስተመጨረሻ አስተያየታቸውን እንዳይሰጡ አልተክለክሉም፡፡ በቅርቡም ቢሆን ጨካኝ እና ሰው በላ የተባለው የደርግም መንግስት ቢሆን "ስልጣኑን የተቀናቀኑትን" ከፍተኛ ወታደራዊ ባለስልጣናቱን በግንቦት 1980 አ/ም የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ሳቢያ ወታደራዊ ችሎት የሞት ቅጣት ሲያስተላልፍባቸው (ውሳኔው እና እርምጃው ትክክል ይሁን እይሁን) ተከሳሾቹ ህጉ በሰጣቸው መብት ላይ ከመናገር አልነፈጋቸውም ነበር ፡፡ታዲያ ዛሬ ህጉን እንተረጉማለን የሚሉ ወገኖች( ዳኞች ) መጽሃፉ ላይ ያለውን የህግ አንቀጽ እንኳን እንብበው ለመፍረድ ሲሳናቸው ስታይ የዚህች ያልታደለች አገር የፍትህ ስርአት ወዴት እያመራ እንደሆነ መገመት አያዳግትም ፡፡"


ጥያቄ፡-እርሶ ታዲያ አሁን ካለው ሁኔታ ሆነ ቀደም ሲል ከተፈጸሙት የህግ ጥሰቶች በመነሳት ከህግ ጋር ተዛማጅነት ያለውን ሙያዎትን እጣፈንታ እንዴት ይመለከቱታል?
አቶ አወቀ፡-"በአገሪቱ ውስጥ ሆነ በውጭ አገር በሚገኙ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ በህግ ሙያ ተመርቀህ አገሬን እና ህዝቤን በሙያዩ አገለግላለው ፡ ቤተሰቤንም በነጻነት አስተዳድራለሁ ማለቱ ዘበት እንደሆነ ሆኖ ነው የሚሰማኝ፡፡ እኔም ብሆን በህግ ትምህርት ላይ ያሳለፍኩት እድሜዩን ወደ ሁዋላ መለስ ብዮ ስመለከተው የባከነ የህይወት ዘመን ሆኖ ይታየኛል ፡፡ ልጆቼን እና ወዳጆቼንም ቢሆን በህግ ነክ ጉዳዩች ዙሩያ ለመማር ከፈለጉ በመ መሪያ ደረጃ ለግላቸው እውቀት ማጎልበት ካልሆነ በቀር በሙያው ዘርፍ ያለማንም አካል ጣልቃ ገበነት እና አስገዳጅነት (በነጻነት) ለመስራት የሚለውን ሙያዊ ምክር አልሰጣቸውም፡፡ " ጥያቄ፡- ሰለ ሰጡኝ ሰፊ ምሁራዊ እና ሙያዊ አስተያየት ከልብ አመሰግንለሁ ፡፡
አቶ አወቀ ፡- "እኔም እድሉን ሰለትሰጠኝ አመሰግናለሁ ፡፡ "


ለተጨማሪ ጥያቄዎች እና መረጃዎች ጽሃፊውን በThis email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ያገኛሉ

ሀገር በምን ይፈርሳል? 2

ተመስገን ደሳለኝ

ከዚህ ቀደም ‹‹ሀገር በምን ይፈርሳል?›› በሚል ርዕስ የዚህን ፅሁፍ የመጀመሪያ ክፍል ፅፌ ነበር። በዚያ ፅሁፍ ላይ ያነሣሁት አንጓ ዘውግ ተኮር የሆነው ፌደራሊዝም ከዕለታት አንድ ቀን ሀገር ማፍረሱ አይቀሬ መሆኑ ላይ ነው። ለዚህም እንደ ‹‹ሠርቶ ማሳያ›› የጉራፈርዳ፣ የጋምቤላ እና የሲዳማ ችግሮች ሊወሰዱ እንደሚችሉ ተነጋግረንባቸዋል። በዚህ ፅሁፍ ደግሞ ከዘውግ ተኮር ፌዴራሊዝሙ በተጨማሪም ዜጎች ‹‹ሀገሬ›› ብለው በሀገራቸው ላይ መተማመን ካልቻሉ ‹‹ሀገር ሊፈርስ›› እንደሚችል እንነጋገራለን። በእርግጥ ይህን ርዕሰ ጉዳይ ደግሜ ለማንሳት ሌላኛው ምክንያቴ ከስርዓቱ የሃሳብ ‹‹ቀሳውስቶች›› ዋነኛው የሆኑት አቦይ ስብሃት ነጋ ሰኔ 16 ቀን 2004 ዓ.ም ከ‹‹አዲስ ጉዳይ›› መፅሔት ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ነው፡፡ ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ