ቱፍ፣ ቱፍ! ጡር አይሁንብኝና ክቡር ጠቅላይ መለስ

ሕሊና አገሬ

ጡር አይሁንብኝና ጠቅላይ አቶ መለስ የታደሉ ነዎት! እውነቴን ነው የለበጣ ወይም የአሽሙር አይደለም። እውነቴን ነው። ”ሰው የተወለደበትን እንጂ የሚሞትበትን አያውቅም” ይላሉ እነዚያ ፈረንጅ ጓደኞችዎት። ሰሞኑን በሚናፈሰው ወሬ የሚሞቱበት ቀን ተተንብይዋል አሉ። ምንኛ ታድለው! ለንስሐ ጊዜን ማግኘት የመሰለ ነገር የለም። የት እንደሚሞቱም ሳያውቁ የሚቀሩ አይመስለኝም። ስለመታደልዎ ወደኋላ እመለስበታለሁ አሁን ስለ ውስጣዊ ሕመም ላንሳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአቶ መለስ መታመምና የዳያስፖራ ፖለቲካ

ግርማ ካሣ

ሰሞኑን ኢትዮጵያውያንን በስፋት እያነጋገረ ያለ አንድ ነገር አለ። እርሱም የጠቅላይ ሚኒሰትር መለስ ዜናዊ መታመም ነው። ምንም እንኳን የመንግሥት ባለሥልጣናት አቶ መለስ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የተለያዩ መግለጫዎች ቢሰጡም፤ አቶ መለስ መሞታቸውን፣ ካልሞቱም ደግሞ ወደ ሥራቸው ሊያስመልሳቸው የሚችል ጤንነት እንደሌላቸው የሚናገሩ ጥቂቶች አይደሉም። በዚህ ሆነ በዚያ፣ በማንም ሰው ላይ ክፉ መመኘት ጥሩ አይደለምና መድኃኒዓለም ባሉበት ቦታ ያስባቸው እላለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከላይ የመጣን ዕድል አለመጠቀም ሞኝነት ነው

ነጻነት ዘገዬ

በሰሞነኛ ሀገራዊ የፖለቲካ ትኩሳትና ያን ተከትሎ ሊከሰት ይችላል ብዬ በጉጉት በምጠብቀው የማይቀር የለውጥ ማዕበል ምክንያት ስሜን የምቀይርበት ዘመን እየባተ እንደሆነ ይሰማኛል። ”ነጻነት ዘገዬ” በሚለው ስሜ የዘለቅሁበት የዓመታት ብሶትም አንገሽግሾኛል። ሲያላዝን የሚኖር ውሻ ብቻ ነው፤ እኔ ደግሞ ሰው ነኝና ከእንግዲህ የማዘንና የመከራ ዘመኔ ወደ ታሪክነት መለወጥ ይገባዋል። እናም ”ወርቁ ሞላ” ወደሚል አዲስ የብዕር ስም እንድሻገር በሀገርም በውጪም ያላችሁ ወገኖች ለጋራ የተሻለ ኅልውና ተረባረቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አልጋወራሽ እንምረጥ ወይስ? (ዳዊት ዋስይሁን)

ዳዊት ዋስይሁን

የተከበረና ጀግናው አበበ ገላው የአቶ መለስን አንገት ካስደፋቸው አንስቶ የሰውየው ስም በየትኛውም ጎራ ባለ የመገናኛ አውታርም ሆነ የማህበራዊ መረብ እስከ አሁን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በሪኮርድ ማለት ይቻላል በየለቱ የመወያያና የመነጋገሪያ ርዕስ ሆኖ እንደሚገኝ የየለት ትዝብት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመለስ አልጋ ወራሾች

Meles Zenawi መለስ ዜናዊ ተስፋዬ ገብረአብ

“መለስ ታመመ” የሚለውን ወሬ ተከትሎ፣ ኮማ ውስጥ መግባቱና መሞቱ እየተነገረ ሰንብቶአል። የወያኔ መንግስት ግን ወሬውን አፍኖ ለመቆየት ተጨናነቀ። መለስ ጀርመን ሃገር ላይ ቀዶ ጥገና ህክምና ማድረጉ በአንድ ወገን ሲገለፅ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ቤልጅየም 10 ቀናት አልጋ ይዞ መሰንበቱ ተሰምቶአል። “አዲሳባ ገባ” የሚለው ተሰምቶ ሳያበቃ፣ “ብራስልስ ላይ መሆኑ ተረጋገጠ” ተባለ። ወሬዎቹ መልከ ብዙና ውል አልባ ነበሩ። ዞረም ቀረ መለስ ታሞአል። ከመለስ መታመም ጋር በተያያዘ እንዲሞትም ሆነ እንዲፈወስ የሚፀልዩ ተደምጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ህወሓት እና የመስዋዕትነት ወጥመድ

ያሬድ አይቼህ

የደርግን ወታደራዊ መንግስት ለማስወገድ በተደረገው ትግል የብዙዎች ህይወት ተሰውቷል። ከቀይ ሽብር ጀምሮ ኢህአዴግ አዲስ አበባን እስከተቆጣጠረበት ቀን ድረስ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የህይወት፣ የአካል፣ የንብረት፣ የእድሜና የስነልቦና መስዋዕትነት ከፍለዋል። ሆኖም ግን መስዋዕትነት መክፈል አንድ ጊዜ ሆኖ የሚያልፍ ክስተት አይደለም - መዘዝም አለው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመሪዎቻችን መልእክት፡ ለዚህ ሰዓት ይመጥን ይሆን?

አለቃ ተክላይ - ካናዳ

ጠቅላይ ሚኒስትሩና ጠቅላይ ተቺው፡

ይሄንን ጽሁፍ የምጽፈው፤ በተወለድኩኝ በ36ኛው አመቴ ዋዜማ ላይ ነው። ሰው በኔ እድሜ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ፤ 21 አመት ሊገዛ ይመቻቻል፤ እነሆ እኔ ደግሞ ጠቅላይ ተቺ ለመሆን ኮምፒውተሬን እስላለሁ። ደግሞ ወገንን። የራስን ወገን፤ የራስን ጎራ፡ መተቸት ይከብዳል። በተለይ አብረው የበሉትን፡ አብረው የጠጡትን፡ አብረው የተሰለፉትን፤ እንዳቅምም ቢሆን የሚችሉትን ለመስራት ደፋ ቀና የሚሉትን። ግን ደግሞ ካልተተቻቸን አናድግም። አንሰለጥንም። ጠላትን የመተቸቱንና የመዘልዘሉን ስራ ሌሎች ሄደውበታል። ስለዚህም፤ እኔ የራስን ጎራ የመተቸቱን አስቀያሚ ሀላፊነት ልወስድ ፈቀድኩ። የዲባቶ ብርሀኑን ቃለምልልስ። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ