የጥቃት ኢላማ የሆነው የሰሜን አሜሪካ የእግር ኳስ ፌደሬሽን (ከሳሙኤል ሽፈራው)

ይህ ፌደሬሽን በሂውስተንና በዳላስ ሁለት ቡድኖች ተመሰረተ። በቀጣዩ አመት ዳላስ ጨዋታው ሲካሄድ ለመጀመሪያ ጊዜ ሜዳ በመሄድ የታደምሁ ነኝ። ይህ ፌደሬሽን ሲመሰረት ሁሉም እንደሚያስታውሰው ከቀይሽብር አምልጠውና ተርፈው የመጡ ስደተኞችና ትቂት በዚሁ በዳላስና ሄውስተን አካባቢ ለትምህርት መጠው የቀሩ ወገኖች የጀመሩት ነበር። በቀጣይ አመታት ከተለያዩ የሰሜን አሜሪካ ከተሞች የተመሰረቱ ቲሞች ወደፌደሬሽኑ በመቀላቀል እድገት እንዲያገኝ አርገውታል። በየአመቱ በአሜሪካ የነጻነት ቀን ሰንበት የሚካሄደው የፌደሬሽኑ የእስፖርት በአል ላለፉት 28 አመታት ለኢትዮጵያውያን ልዩ የሆነ የአመት በአል በመሆኑ፤ ሳምንቱን ብዙ ወገኖች በጉጉት ይጠብቁታል። በ1980 ወቹ አመታት አገራችን በደርግ ስርአት ስር ስለነበረች፤ በጊዜው የነበረው አንባገነን ይህን ፌደሬሽን በክፉ ይመለከተው እንደነበርም የሚዘከር ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

20 ዓመት ስንት ነው

ግርማ ደገፋ ገዳ

ኢሜይል አስጠላፊ፣ ገዢውን ማኳኳያ ራዲዮ አየር ባለቤት፣ የማወናበጃ መጽሔት አዘጋጅ፣ የተዘረፈ ዶላር አስተላላፊ፣ የፕሮፓጋንዳ ለቅላቂ፣ የሚሰረቅ እቃ ኤክስፖርተር፣ በልማት ስም የዘረፋ አማካሪ፣ የራቁት ዳንስ ቤት ባለቤት፣ የጸጥታ ሰራተኛና ወሬ አመላላሽ ሆነው ኢሕአዴግን ከሚያገለግሉት መሃል፤ አብዛኛዎቹ ሚሊዮነር ናቸው። እነዚህ ሰዎች፣ በሕዝብ ስም ተለምኖ ከሚመጣው ገንዘብ ላይ ድርሻቸውን ለማፈስ ብለው፤ ኮቴያቸው ባሪያ እንዲሆን ፈቅደዋል። በዛሬው ጽሁፌ፣ የዘረፋ ጥቅማቸውን እያስጠበቁ መንግሥትን ስለሚያኳኩሉ፣ ስለዘራፊው መንግሥትና የፍትህ ሥርዓቱ ውስጥ ተወሽቀው ስለሚያሾፉ ዳኞች በጥቂቱ የምለው ይኖረኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ሥልጣኔ መነሻው፣ ጉዞውና መድረሻው (ጌታቸው ኃይሌ)

መግቢያ

የዓባይ ወንዝ ከምንጩ ላይ ትንሽ ነው፤ ከብዙ የኢትዮጵያ ታላላቅ ወንዞች አይበልጥም። ኢትዮጵያን ሲለቅ ግን ግዙፍ ሆኖ ነው። ምንም እንኳ"ዓባይ" ቃሉ አንስታይ ጾታ ("ትልቂት" ማለት) ቢሆንም ወንዙ በዚህ ስም የተጠራው ይኸንን ትልቅነቱን ለማመልከት ሳይሆን አይቀርም። (ሙሉውን ጽሁፍ በፒ.ዲ.ኤፍ ለማንበብ ይህንን ይጫኑ)

ወግ ነው ሲዳሩ ማልቀስ ይባል ነበር ዱሮ ወግ ነው ምርጫ ማሸነፍ ሆነ ዘንድሮ!

ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም

አስተሳሰብና ጉልበት (ሕገ አራዊት)

በረከትን በደንብ የሚያውቀው ያሬድ ጥበቡ ሙልጭ አድርጎ ነግሮታል፤ ያሬድ ከዚህ በፊትም ስለበረከት ጽፎ ነበር፤ አሁን ከጻፈው ጋር ሳስተያየው አንድ ግጥም ትዝ ይለኛል፤ አንዲት የቸገራት ሴትዮ ያንጎራጎረችው ይመስለኛል፡-

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአፍሪካ አባት አጼ ኃ/ስላሴ እንጂ ክዋሜ ንክሩማ አይደሉም!

ያዕቆብ ኃይለ ማርያም (/)

አፍሪቃውያን በአረቦች እየተፈነገሉ ለነጮች ተሽጠው ባህር ሲሻገሩ ንብረታቸውም ወደ አውሮፓና አሜሪካ ሲጋዝ ብዙ ምዕተ ዓመታት እንዳስቆጠሩና ከሃያ ሚልዮን ያላነሱ አፍሪቃውያን በዓለም ዙሪያ እንደተበተኑ ታሪክ ዘግቦአል። እነዚህኑ አፍሪቃውያን ባህር ማዶ ለማሸጋገር፣ በመርከብ ውስጥ ከታጨቁበት ቀን አንስቶ የተለያዩ ግብታዊ አመጽ ቢያካሄዱም ወደ ካሬ ቢያን የተጋዙት ባሮች እንዲሁም ዘግይተው ነፃ የወጡት ተሳብስበው በ18ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ መላው ጥቁር አቀፍ የነፃነት እንቅስቃሴ (PANAFRICANISM) ጀመሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ እንደ ሩዋንዳ? የዳዎድ ቡድን ባወጣው መግለጫ ላይ

ግርማ ካሳ

መግቢያ

በጄኔራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ «ኦሮሞ የኢትዮጵያ ግንድ ነው። ቅርንጫፍ ከግንድ ይገነጠላል እንጂ ግንድ ከቅርጫፍ አይገነጠልም» በሚል፣ የኢትዮጵያን አንድነት ተቀብሎ፣ ለኦሮሞ ባህልና ቋንቋ መስፋፋት፣ ለዜጎች ሁሉ መብት መከበር፣ ከተቀረው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጎን በመቆም ትግሉን እንደሚቀጥል ይፋ አድርጓል። ይህ ከኦነግ ዘንድ ይፋ የተደረገው የፖለቲካ አቋም ለውጥ፣ ኦሮሞ ነን የሚሉትን ጨመሮ በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዘንድ ከፍተኛ ውይይትን ጭሯል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቻይና ደንደስ… እኛ እንወደስ

አቤ ቶክቻው

ከመጀመሪ በፊት… በተለያየ ግዜ በተለያየ መልኩ ተግቼ እንድፅፍ ያገዛችሁኝ እና፤ “አይዞህ ከጎንህ ነን” ያላችሁኝ ወዳጆቼ በርካታ ናችሁ። እኔም የወዳጆቼን አጋርነት ባየሁ ግዜ ደስ ብሎኛል። እናም በድጋሚ “አለንልህ!” እንዳላችሁኝ አንድዬ አለሁ ይበላችሁ ብዬ ወደዛሬው ወግ አሳልጣለሁ … ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግልጽ ደብዳቤ (ፀሐይ አሳታሚና ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ) – (ሊያነቡት የሚገባ)

ክፍሌ ሙላት (የኢነጋማ ፕሬዝዳንት) - በግል

ሲሞላልኝ በሳምንት ካልሆነልኝ ደግሞ በአስራ አምስቱ ሰላምታዬን ካሉበት የማደርሳቸው ወዳጆች አሉኝ።  ለአገር ምድሩ ሳይሆን በጣት የሚቆጠሩ። ከእነዚህ መካከል አንዱ የሙያ ባልደረባዬ ኤልያስ ወንድሙ ነው። ትውውቃችን የመንገድ ላይ አይደለም። የኔዎቹ የነፃ ፕሬስ አባላትና የሃገሬ ሰላም ወዳድ ኃይሎች በግፈኞቹ የሕወሃት አባላትና ሹመኞች የሚሰደዱበት የሚታሰሩበት ብሎም የግፍ ፅዋ የሚቃመሱበት በእነዚያ የትግል፣ የፈተናና የፍልምያ ዓመታት የልብ ወዳጅና ለእውነት የቆሙ በመብራት በሚፈለጉበት የወያኔ የግፍ ዘመናት። ዛሬም ይህ ሐቅ ገሃድ ነው። ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ