የአንበሳ ልጅ ሳለ የጅብ ልጅ ገነነ፣ አላስበላም አለ ጸጉሩ እየበነነ
ይገረም አለሙ

ነገር በምሳሌ
ጠጅ በብርሌ፣
ይሉ የነበሩቱ
አበው እና እመው እነዛ የጥንቱ፣
እንደ አሁኖቹ ቃላት ሳይደርቱ
ዙሪያ ጥምዝ ሄደው ነገር ሳይጎትቱ፤
በምሳሌ አዋዝተው በስንኝ ቋጥረው
በሁለት መስመር ቃል - ቅኔ ተቀኝተው፤
ምክረ ነገራቸው - ከጆሮ ደጃፍ ነጥሮ ሳይመለስ
ከውስጠ ልቦና ከአዕምሮ እንዲደርስ፤
አድርገው ነበረ የሚያስተላልፉት
ሳይወርሰው ቀረ እንጂ ይሄ ትውልድ ንቆት፤
አልፎ አልፎ ለጽሁፌ የአበውን አባባል የምጠቀመው በሁለት ምክንያት ነው። ዋናውና የመጀመሪያው ምክንያቴ አባባሉ መልዕክቱ ጥልቅ ይዘቱ ምጥቅ የሆነና ዘመን ባዘመነው ይሁን ባደነዘዘው የእኛ ብዙ ደቂቃዎች የሚወስድ አገላለጽም ሆነ ቢጻፍም ገጽ የማይበቃውን ነገር መረዳት ለሚችልና ለሚፈልግ ሰው በአጭር የሚገልጽ በመሆኑ ነው። ሁለተኛው ሥልጣኔ የራስን እየተዉ፤ በተውሶ ነገር መኮፈስ ማለት ይመስል እንኳን ለልጆቻውን ሊያስተምሩ ለራሳቸውም ወግ ባህላቸውን የአነጋገር ዘያቸውን እየረሱ ላሉት ወገኖች በእግረ መንገድ ማስታወስ ከተቻለ በሚል ነው። ፕ/ር አዱኛ ወርቁ ጥርት ባለው አገርኛ አነጋገር ሲናገሩ፤ ሰለጠን ባዮቹ ቢከፍቱ ተልባዎች ብዙ እንደሚሉ ባውቅም፤ እኔ ግን እንዴት እንደምኮራባቸውና እንደምቀናባቸው እኔና እኔ ነን የምናውቀው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...

![የሕዝብ ተቃውሞ በገዥው ፓርቲ ላይ። [ፎቶ፣ Reuters] Protests accusing the Ethiopian government](/amharic/images/doc/images/articles/2017/170525-protests-accusing-ethiopian-government.jpg)









