ሰመሃል መለስ የገባት መተካካት - ተቃዋሚዎች ያልገባቸው መታደስ!

ክንፉ አሰፋ

Semehal Meles

የአፈና ግዜ አዋጁን ተከትሎ፤ የህወሓቱ ፋና ብሮድካስቲንግ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያስተናገደው "የውይይት መድረክ" አዳዲስ ኩምክናዎችን ይዟል። ልደቱ አያሌውን በመሪ ተዋናይነት ያሳተፈውን ይህን አዲስ የበረከት ስምዖን ድራማ ብዙም ሰው አላየውም። ህዝቡ ፋና ሚባል ነገር እንደሬት መርሮታል። ገሚሶች ደግሞ በ"ቃና"ው "ጥቁር ፍቅር" ድራማ ተጠምደዋል። በዚህ ድራማ ልደቱ አያሌው መሪ ገጸ-ባህሪይ ተላብሶ ይተውን እንጂ፤ እንደወትሮው ቀልብ ሊስብ አልቻለም። በኢትዮጵያ ታሪክ ወያኔ መድብለ ፖርቲን የፈቀደ ድርጅት እንደሆነ በሙሉ አፉ ሲናገር እሱ አላፈረም። ከሱ ይልቅ የተሸማቀቁት እነ በረከት እና ስብሃት ናቸው። በልባቸው አበስኩ ገበርኩ እያሉ ... ጌታዎቹ ኀዘን ሲሰማቸው እሱ ያለቅሳል። በዚህ አቋሙ ከሦስተኛው መንገድ ወደ አንደኛው የተሸጋገረ ይመስላል ልደቱ። ለነገሩ እንጂ፤ ለሱ መገለባበጥ አዲስ ጉዳይ አይደለም!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ሳይካተቱ የተረሱ አንቀጾች

አሰፋ ዳሞቴ (ከአዲስ አበባ)

The forgotten chapters in the state of Emergency

በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ውስጥ ሆነን ሁለተኛ ሣምንታችንን ያዝን። ዕድሜ ለአዋጁ ገንዘቤም አፌም ዐረፉ። አሁን አፌን ሰብስቤ በጊዜ ወደቤቴ ከማምራቴ በፊት በየመሸታ ቤቱ እንደጣቃ ስቀደድ አመሽ ነበር። አንዱ ጆሮ ጠቢ ጠልፎ ቢወስደኝና ድራሼን ቢያጠፋው ለምግብ ያላነሱ ለሥራ ያልደረሱ ልጆቼ ወደ በረንዳ መበተናቸው አይቀርም። በሌላም በኩል አዋጁን ቀድሞ በተዘጋው ኢንተርኔት ሰበብ ብዙ ገንዘብ በቴሌ እበላ ነበር፤ አሁን ግልግል ነው። ሣር አልበላም እንጂ፤ በዚያም ላይ “እምቧ!” እያልኩ እንደከብቶቹ አልጮህም እንጂ፤ ዕድሜ ለህወሓት የለዬልኝ የቤትና የዱር እንስሳ ሆኛለሁ - በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አንድ አይሉ ሁለት ዲፕሎማ ይዤ የማልናገር የማልጋገር የወያኔ ጥፍጥፍ ባሪያ ሆኜ መገኘቴ፤ የሰው ልጅ የደረሰበትን ኢትዮጵያዊ የዕድገት ደረጃ ያመለክታል። ግሩም ዕድገት! ግሩም እንከን የለሽ ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያዊ ሩህሩህ መንግሥት!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፈጣሪና የህዝብ ዓይኖች በናንተ ላይ ናቸው!

ዮፍታሔ

GODs eye

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጃችኋል።

በግልጽ አፋኝ የሆነ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አፈጻጸምና ዝርዝር ደንብም አውጥታችኋል።

ከዚህ ቀደም ሁሉን አድራጊው ራሱ ያልሆነ ይመስል፤ "ኮማንድ ፖስቱ የሀገር መከላከያ ኃይል፣ የፌዴራል ፖሊስ እና የክልል መንግሥታት ልዩ ኃይሎችን ያካተተ" መሆኑንም በመግለጽ አላግጣችኋል።

እንዲህም ሆኖ የራሳችሁን ሕገ-መንግሥት ታከብሩ ከሆነ ሌላ የሚቀራችሁ ነገር አለ። እንደማይጠቅም ብናውቅም በሰነድ ይይዘው ዘንድ ህዝቡ ይከታተላችኋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"አንድ ኢትዮጵያ! አንድ ሀገር! አንድ ህዝብ!" ምን ማለት ነው?

ሸንቁጥ አየለ

Out of Many WE are ONE!

ኢትዮጵያ በምልዓት ድና እና ተፈውሳ ማዬት የምትፈልጉ ኃይላት "አንድ ኢትዮጵያ! አንድ ሀገር! አንድ ህዝብ!" የሚለውን የአስተሳሰብ አድማስ እንዳትለቁ። ለነገሩ ይሄ አስተሳሰብ ከተሸነፈ ቆዬ። የፀረ-ኢትዮጵያዊነት ኃይላት በመጀመሪያ ወደ ምድር ከስክሰው በእግራቸው የረገጡት እና ያስረገጡት ይሄን አስተሳሰብ ሐሰት ነው በማለት ነው። የአንድን ወገን ጥቅም ለማስጠበቅ የሚነፋ ፕሮፖጋንዳ ነው በሚል ሐሰተኛ ቀመር ተነስተው ነው ውድቅ ያደረጉት። የኢትዮጵያ ህዝብ ምንም አንድነት የለውም ብለው ተነስተው ይሄው ዛሬ ሀገሪቱን የህልውናዋ ማክተሚያ ወደ ሆነ አፋፍ ላይ ገፍተዋት ከፍተኛ ትርምስ ውስጥ ጥለዋታል። ከዛሬው ትርምስ ይልቅ የነገው ትርምስምስ ይበልጥ አሳሳቢ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወያኔ ሊታደስም ሊታከምም የሚችል ኃይል አይደለም! መወገድ ያለበት እንጂ!

ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

“በገሃነም ውስጥ እጅግ የሚያቃጥለው ቦታ የተያዘላቸው፤ የሞራል ቀውስ በሚታይበት ወቅት ለህዝብ ወገናዊነትን ለማያሳዩ ሰዎች ነው።” Dante

Bereket Simon

መግቢያ

ሰሞኑን ወያኔ የሚያወናብደው ራሱን ለማደስ እንደተዘጋጀና ጊዜም እንደሚያስፈልገው ነው። በአገዛዙ ውስጥ የአስተዳደር ብልሹነት አለ፣ የኪራይ ሰብሳቢነት ባህል ተስፋፍቷል፣ ሙስና ለቢሮክራሲው ማነቆ በመሆን ሥራ አላሠራም በማለት የሀገርን ዕድገት እየጎተተ እንደሆነ እየመላለሰ ይነግረናል። እነዚህንና ሌሎች የአስተዳደር ብልሹዎችን በየስብሰባውና በቴሌቪዥን “የውይይት መድረከ” ላይ የሚያወሩልን የአገዛዙ የመሪ ቁንጮዎች በሽታዎቹ ከሰማይ እንደወረዱ እንጂ እነሱ ለአጋዛዛቸው እንዲያመቻቸው ሆን ብለው የፈጠሩትና ከተበላሸ ኢ-ሳይንሳዊና ሀገር አፍራሽ የአሠራር ዘዴ ጋር እንደተያያዘ አድርገው አይደለም የሚያቀርቡት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የለውጥ ኃይሎች” ግልፅና ደፋር ውይይት ለመፍትሔና የጋራ ድል (ኤርሚያስ ለገሰ)

Ermias Legesseለህዝብ የውይይት መድረክ የተዘጋጀ (ቺካጎ/ኢሊኖይ)

ኤርሚያስ ለገሰ

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ራዲዮ(ኢሳት)

ጥቅምት/2016

ማስታወሻ

*ይህ ጽሁፍ ከራሴ ውጭ የምሰራበትን የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንና ሬዲዮ (ኢሳት)ን ጨምሮ የማንንም አቋም አያንፀባርቅም።

**"የአዲስ አበባ ነዋሪ" ("አዲስ አበቤ") የሚለው ቃል ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ሆኖ በአዲስ አበባ የሚኖር አሊያም ለወደፊት የመኖሪያውን አዲስ አበባ ለማድረግ የፈለገን በሙሉ የሚያጠቃልል ነው።

መንደርደሪያ

የዛሬ ሦስት ወራት አካባቢ ከኦሮሞ አክቲቪስት ገረሱ ቱፋ ጋር በኢሳት ስቱዲዮ ለአጭር ሰዓታት ኢ-መደበኛ ወግ ጠርቀን ነበር። ገረሱ በወጋችን መሀል “ለጋራ መፍትሔ ግልፅና ደፋር ውይይት የማድረጊያው ሰዓት አሁን ነው” በማለት ይናገር ነበር። መልሶ መላልሶም “የጋራ ችግር አለብን፤ ያልተነጋገርናቸው እና በይደር ያቆየናቸው ድፍረት የሚጠይቁ አጀንዳዎች ከፊታችን ተቆልለዋል። በግልፅና በሐቅ ተወያይተን መፍትሔ ልናበጅለት ይገባል” እያለ የቀጣይ ስጋቱን ይዘረዝር ነበር። የዛሬን ብቻ ሳይሆን የነገንም ጭምር። የነገንም ብቻ ሳይሆን የተነገወዲያውም። ለልጅና ልጅ ልጆቻችን!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጃዋር ቻርተር

ይገረም አለሙ

Jawar Mohammed

መንደርደሪያ

ጃዋር የኦሮምያን ቻርተር እያዘጋጀን ነው በማለት የተናገረው ዋንኛ የመነጋገሪያ ብቻ ሳይሆን፤ የመነታረኪያም ርዕሰ ጉዳይ ሆኗል። ከሚያግባባን ይልቅ በሚያለያየን ላይ ጎራ ለይቶ የመነታረካችን አንዱና ዋናው ጉዳይ ወይ ከዚህ ወይ ከዛ የሚለው መሃል ላይ ቦታ የሌለው ወይንም የማይሰጠው ፖለቲካችን ነው። ሁለተኛው ችግራችን ደግሞ ድጋፋችን ነፋስ አይንካህ የሚል ነቀፌታችን መልካም ጎኖችን የማይመለከት መሆኑ ነው። ይሄ በፍጹም አይበጅም የምንወደውንና የምናደንቀውን ልንተቸውም ሆነ ልንመክረው፤ የማንወደውንና የማንደግፈውን ደግሞ ብዙ ስንነቅፈው ለበጎ ሥራው በትንሹም ቢሆን ጎሽ ልንለው ይገባል። ነቀፌታም ሆነ ትችታችን ወደ መሃል የሚጎትት እንጂ ወደ ዳር የሚገፋ መሆን የለበትም፤ ከስህተት ለመማር ከጥፋትም ለመቆጠብ የሚያበረታታ እንጂ፤ ጥላቻን የሚያስፋፋና እልህ ውስጥ የሚያገባ መሆን አይኖርበትም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፌስቡክን እንደምክንያት

ኃብተወልድ ተሾመ

Facebook banned in Ethiopiaሀገሬ ይህን ጊዜ ባታይ እመርጥ ነበር፤ ከ54 የአፍሪካ ሀገራት በህዝብ ብዛት ናይጄሪያን ቀጥላ በሁለተኝነት የምትቀመጠው ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ሁኔታ ባለፉት ሩብ ክፍለ ዘመን ዕይታ የማታውቀው አይነት ነው። በየቦታው በየአካባቢው ወጣቶች ይታሰራሉ፤ ወጣቶች ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች ይፈጸምባቸዋል፤ ባስ ሲልም አንዲት ሕይወታቸውን የሚያጡበት ጠያቂ የበዛበት መልስ የሌለበት ዘመን ላይ ደርሰናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ርጥቡ ሬሳ ደረቅ ያስነሳ

ይገረም አለሙ

Eng. Hailu Shawel and Prof. Asrat Woldeyes

ዛሬ ጥቅምት አንድ ቀን 2009 ዓ.ም. ቀትር ላይ በሞት የተለዩንን ኢ/ር ኃይሉ ሻውልን ወደ ዘለዓለማዊው ቤት ለመሸኘት አዲስ አበባ አራት ኪሎ ከሚገኘው ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን ተገኝተናል። እዛው የተገናኘን ሰዎች ዝናቡ መቆሚያ ቢያሳጥንም አንድ ጥግ ይዘን አስክሬናቸው እስኪደርስ ወግ ይዘናል። ኢ/ር ኃይሉን ለመጀመሪያ ግዜ ያወቅናቸው በመአህድ ከዚያም በመኢአድ ቀጥሎም በቅንጅት፤ እንደገና ተመልሶ በመኢአድ በመሆኑ ከዚህ እውቀታችን በመነሳት ከፊት ወደ ኋላ እያስታወስን ስናነሳ ስንጥል የመአህድ መስራችና ፕሬዝዳንት የነበሩትንና በእስር ተሰቃይተው በግፍ የሞቱትን ፕ/ር አስራት ወልደየስን አስታወስን። የገደሉንንም የሞቱልንንም እኩል የምንረሳ ምን ጉዶችን በማለትም ራሳችንን ወቀስን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ዓላማ ምንድን ነው?

ዮፍታሔ

Getachew Ambaye. ጌታቸው አምባዬ

- ችግሩ የተፈጠረው በኦሮሚያ እና ምናልባትም በአማራ ሆኖ እያለ በመላ ሀገሪቱ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ተግባራዊ ማድረግ ለምን አስፈለገ?

- ኦሮሚያና አማራ ከዚህ ተመሳሳይ በሆነ ወታደራዊ ዕዝ (Martial law) ቆይተዋል። ህዝባዊ እምቢተኝነቱን ግን አላቆመውም። ይህ ከሆነ ይህን አዋጅ ማወጅ ለምን አስፈለገ?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ