ሰመሃል መለስ የገባት መተካካት - ተቃዋሚዎች ያልገባቸው መታደስ!
ክንፉ አሰፋ

የአፈና ግዜ አዋጁን ተከትሎ፤ የህወሓቱ ፋና ብሮድካስቲንግ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ያስተናገደው "የውይይት መድረክ" አዳዲስ ኩምክናዎችን ይዟል። ልደቱ አያሌውን በመሪ ተዋናይነት ያሳተፈውን ይህን አዲስ የበረከት ስምዖን ድራማ ብዙም ሰው አላየውም። ህዝቡ ፋና ሚባል ነገር እንደሬት መርሮታል። ገሚሶች ደግሞ በ"ቃና"ው "ጥቁር ፍቅር" ድራማ ተጠምደዋል። በዚህ ድራማ ልደቱ አያሌው መሪ ገጸ-ባህሪይ ተላብሶ ይተውን እንጂ፤ እንደወትሮው ቀልብ ሊስብ አልቻለም። በኢትዮጵያ ታሪክ ወያኔ መድብለ ፖርቲን የፈቀደ ድርጅት እንደሆነ በሙሉ አፉ ሲናገር እሱ አላፈረም። ከሱ ይልቅ የተሸማቀቁት እነ በረከት እና ስብሃት ናቸው። በልባቸው አበስኩ ገበርኩ እያሉ ... ጌታዎቹ ኀዘን ሲሰማቸው እሱ ያለቅሳል። በዚህ አቋሙ ከሦስተኛው መንገድ ወደ አንደኛው የተሸጋገረ ይመስላል ልደቱ። ለነገሩ እንጂ፤ ለሱ መገለባበጥ አዲስ ጉዳይ አይደለም!
ሙሉውን አስነብበኝ ...



ለህዝብ የውይይት መድረክ የተዘጋጀ (ቺካጎ/ኢሊኖይ)
ሀገሬ ይህን ጊዜ ባታይ እመርጥ ነበር፤ ከ54 የአፍሪካ ሀገራት በህዝብ ብዛት ናይጄሪያን ቀጥላ በሁለተኝነት የምትቀመጠው ኢትዮጵያ አሁን ያለችበት ሁኔታ ባለፉት ሩብ ክፍለ ዘመን ዕይታ የማታውቀው አይነት ነው። በየቦታው በየአካባቢው ወጣቶች ይታሰራሉ፤ ወጣቶች ኢ-ሰብዓዊ ድርጊቶች ይፈጸምባቸዋል፤ ባስ ሲልም አንዲት ሕይወታቸውን የሚያጡበት ጠያቂ የበዛበት መልስ የሌለበት ዘመን ላይ ደርሰናል።




