ታላላቅ የታሪክ ክህደቶች ከ“ፍኖተ ገድል”

ፍኖተ-ገድልገብረመድህን አርአያ (ተጻፈ ሚያዝያ 6, 2004 ዓ.ም.)

ለአንድ ሰሞን ለአመታት በአሜሪካኗ ግዛት ኦሃዮ ውስጥ በስደት ሲኖር የነበረው የወያኔ ነባር ታጋይ፣ በስለላ የሰለጠነ … እና መሪህ ባኽታ ብስራት አማረ የጻፈው መጽሃፍ በህትመት ወጥቶ ጉድ፣ ጉድ ከተባለለት በኋላ እኔም እንደ ኢትዮጵያዊነቴ እና እንደ ቀድሞ የህወሃት ቀዳሚ ታጋይነቴ መጽሃፉን አግኝቼ ለማንበብ እና የግሌን ግምገማ ለማድረግ መፈለጌ አልቀረም። ዘግይቶም ቢሆን መጽሃፉ በእጄ ገብቶ የማንበብ እድል አገኘሁ። መቼም ጉድ ነው የሚባለው!! ህወሃት እና በዙሪያው የከበቡት ጉዶች የቅጥፈት እና የክህደት ጉድ ማለቂያ የለውም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እልፍ አንድ ሺህ ወይስ ዐሥር ሺህ?

ካሣሁን ዓለሙ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

፩. ምክንያተ ጽሕፈት

ይስማዕከ ወርቁ በቅርብ ጊዜ ባሳተመው ‹ተከርቸም› በሚለው 6ኛ መጽሐፉ ‹እልፍ (፼) ዐሥር ሺህን ሳይኾን አንድ ሺህን ይወክላል› የሚል መከራከሪያ አቅርቧል። እኔም በመጽሐፉ ያቀረበውን የእልፍ(፼) ቁጥር አስተያየት ከተመለከትኩ በኋላ መስተካከል ያለበት ጉዳይ መስሎ ስለተሰማኝ ይህንን ጽሑፍ በተወሰነ ደረጃ ሞነጫጭሬ አስቀምጨው ነበር፤ በዕንቁ መጽሔት ተጠይቆ የሰጠውን መልስ ከተመለከትኩ በኋላ ግን መከራከሪያ ነጥቦችን ማቅረብ አስፈላጊ መስሎ ታየኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የዓለማየሁ ታዬ አዲስ የልጆች መጽሐፍ

Betsy and the Supercopter - By Alemahehu Tayeዓለማየሁ ዲባባ

ለልጆች ከሚዘጋጅ ጽሑፍ አኳያ ሲዳሰስ

ዓለማየሁ ታዬ ገጣሚ፣ ተርጓሚና ጋዜጠኛ ነው። ከዚህ ቀደም በአይነታቸውና በይዘታቸው ልዩ የሆኑ ሦስት የግጥም መድብሎችን እንዲሁም የልጆች መጻሕፍት ተርጉሞ ለሕትመት አብቅቷል። በቅርቡ ደግሞ ወጥ የሆነ አንድ የልጆች መጽሐፍ በእንግሊዝኛ ቋንቋ አሣትሟል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የበረከት መጽሐፍ

የሁለት ምርጫዎች ወግ Yehulet Mirchawoch Wog ተስፋዬ ገብረአብ This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

የበረከትን መጽሐፍ አነበብኩት …

በእውነቱ ህትመቱ ቆንጆ ነበር። ሽፋኑ እንደ ሃብታም ጉንጭ ይለሰልሳል። ከቻርልስ ዲክንስ ታዋቂ መጽሐፍ የተኮረጀ ቢሆንም ርእሱም ቢሆን አሪፍ ነው - የሁለት ምርጫዎች ወግ። የበረከትን መጽሐፍ ያሳተመው መሐመድ አሊ አልአሙዲ የተባለው ነጋዴ መሆኑን ፍትህ ጋዜጣ ላይ አንብቤ ነበር። መጽሐፉ 314 ገፆች እና 10 ምዕራፎች ይዞአል። ዋጋው 90 ብር ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሁለቱ ‹‹ኢህአፓ››ዎች ጉራማይሌ ወግ (በረከት ስምኦን እና ብርሃኑ ነጋ)

ተመስገን ደሳለኝ

ከኢህአፓ ወደ ኢኮፓ፤ ከኢኮፓ ወደ ኢህዴን፤ ከኢህዴን ወደ ብአዴን… እነዚህ ሁሉ የዛሬው እንግዳችን የፖለቲካ ዝውውሮች ናቸው። መቼም ‹‹በዚህ ትውልድ›› ዝውውር ተፈፀመ ወይም ተዘዋወረ ከተባለ ከማንችስተር ዩናይትድ ወደ ሪይል ማድሪድ፤ አሊያም ከአርሰናል ወደ ባርሴሎና ነው። ‹‹በያ ትውልድ›› ደግሞ ከአንዱ ፓርቲ ወደ ሌላው ፓርቲ፤ ከሶሻሊዝም ወደ ካፒታሊዝም፤ ከኢምፔሪያሊዝም ወደ ኮሚኒዝም፤ ከአልባኒያኒዝም ወደ ማሌሊትዝም፤ ከማሌሊትዝም ወደ አብዮታዊ ዲሞክራቲሲዝም … ሲሆን ይሄ አይነቱ ዝውውር ‹‹የብልህ›› ስልት ተደርጎ ከመወሰዱም ባሻገር ለተዘዋዋሪዎቹ ጫማ ከመቀየር የቀለለ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሸራተኑ ምሽት - በአቶ በረከት መጽሐፍ

የሁለት ምርጫዎች ወግ Yehulet Mirchawoch Wogአዲስ አድማስ ጋዜጣ

- አቶ በረከትና ሼኽ መሐመድ አሊ አልአሙዲ የተደናነቁበት ምሽት

- አቶ መለስ፣ ኢህአዴግና አልአሙዲ ተወድሰዋል

- ኢህአዴግ “የሕዝብ ፍቅር ያለው ፓርቲ” ተብሏል

- በመጽሐፉ ተቃዋሚዎች ክፉኛ ተተችተዋል - በተለይ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

የኢህአዴግ ነባር ታጋይ፣ የቀድሞው የማስታወቂያ ሚኒስቴር፤ አሁን ደግሞ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር እንዲሁም በምርጫ 97 ጉልህ ስፍራ የነበራቸው አቶ በረከት ስምኦን ጻፉት የተባለውን መጽሐፍ ለማንበብ በጉጉት ስጠባበቅ ነበር። ባለፈው ማክሰኞ በመጽሐፉ ምረቃ ላይ ለመታደም ወደ ሸራተን አዲስ ሆቴል ያመራሁትም ከዚህ ጉጉት በመነጨ ስሜት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ