በአ.አ. ውጭ ጉዳይ መ/ቤት አካባቢ በደረሰ ፍንዳታ ሦስት ሰዎች ሞቱ

ሁለት ቆሰሉ፣ አምስት ተረፉ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ግንቦት 12 ቀን 2000 ዓ.ም. May 20, 2008)፦ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ውስጥ በሚገኘው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት አካባቢ ሚኒባስ ውስጥ በተከሰተ ፍንዳታ የሰው ሕይወት ማለፉን ከአዲስ አበባ ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ጥቆማ አስረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ኩማ ደመቅሳ የአዲስ አበባ ከንቲባ ሆነው ተሾሙ

Ato Kuma DemeksaEthiopia Zare (ማክሰኞ ግንቦት 12 ቀን 2000 ዓ.ም. May 20, 2008)፦ ኢህአዴግ ባለፈው ሚያዝያ 5 እና 12 ቀን 2000 ዓ.ም. በተካሄዱት ምርጫዎች ብቻውን ተወዳድሮ ካሸነፈ በኋላ በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ምክር ቤት መስራች ጉባዔውን አካሂዶ ከንቲባውንና ቀሪዎቹን ባለሥልጣናት መምረጡን ከአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ዛሬ ሪፖርተር ዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ግንቦት 23 ጠቅላላ ጉባዔውን ያካሂዳል

Ethiopia Zare (ሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2000 ዓ.ም. May 19, 2008)፦ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ትናንት ባካሄደው የላዕላይ ምክር ቤት ስብሰባው ግንቦት 23 ቀን 2000 ዓ.ም. ጠቅላላ ጉባዔውን ለመጥራት መወሰኑን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ወገኖች ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የላዕላይ ም/ቤት ነገ ይሰበሰባል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ግንቦት 9 ቀን 2000 ዓ.ም. May 17, 2008)፦ በወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራው የቀድሞው የቅንጅት ፓርቲ፣ የአሁኑ የ”አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ” በነገው ዕለት የላዕላይ ም/ቤቱ ተሰብስቦ ፓርቲው ሕጋዊ ፈቃድ ለማግኘት ያስችለው ዘንድ ወሳኝ የሆኑ ውሳኔዎች ላይ እንደሚደርስ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የመያድ” ረቂቅ ዐዋጅ የሞት ቅጣት ነው ተባለ

መያዶች ለፍትህ ሚኒስቴር አቤቱታ አቀርበዋል

Ethiopia Zare (ዓርብ ግንቦት 8 ቀን 2000 ዓ.ም. May 16, 2008)፦ መንግሥታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች (መያዶች) “የበጎ አድራጎት ድርጅቶችና ማኅበራት ረቂቅ ዐዋጅ” በሚል የቀረበው ረቂቅ በመያዶች ላይ የተሰነዘረ የሞት ቅጣት ነው በሚል በባለድርሻዎቹ ተተቸ። ረቂቁ ለፓርላማ ከመመራቱ በፊት፣ ሰፊ ውይይት ሊደረግበት እንደሚገባም በመግለጽ ለፍትህ ሚኒስቴር አቤቱታ አቅርቧል ሲል ‘እንቢልታ’ የተሰኘው በሀገር ውስጥ የሚታተም ጋዜጣ በዛሬው ዕትሙ ዘገበ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግንቦት ሰባት የተጠራው ሰልፍ በስቶክሆልም ተካሄደ

በማትያስ ከተማ

Ginbot 7 Rally  - Stockholm, Sweden

Ethiopia Zare (ኀሙስ ግንቦት 7 ቀን 2000 ዓ.ም. May 15, 2008)፦ ግንቦት ሰባት ቀን 1997 ዓ.ም. የተደረገውን የዲሞክራሲ ትግል ለማስታወስና በወቅቱ የተሰዉትን ሰማዕታት ለመዘከር በዛሬው ዕለት ግንቦት 7 ቀን 2000 ዓ.ም. (ሜይ 15 ቀን 2008) ሊደረግ ታቅዶ የነበረው ሰልፍ በስዊድን ዋና ከተማ በስቶክሆልም ተደረገ። በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን አዘጋጆቹ ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ገለጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነዶ/ር ብርሃኑ ነጋ "ግንቦት 7" ንቅናቄን በይፋ አሳወቁ

Ethiopia Zare (ረቡዕ ግንቦት 6 ቀን 2000 ዓ.ም. May 14, 2008)ዶ/ር ብርሃኑ ነጋን ጨምሮ አምስት የቀድሞ የቅንጅት የላዕላይ ምክር ቤት አባላት ስላቋቋሙት "ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ" በተሰኘው አዲስ የፖለቲካ ፓርቲን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ኔትዎርክ (ኢ.ቲ.ኤን.) መግለጫ ሰጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኀሙሱ ዓለም አቀፍ ሠላማዊ ሰልፍ በስዊድን የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ይካፈላሉ

Reported by Matias Ketema

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ግንቦት 5 ቀን 2000 ዓ.ም. May 13, 2008)፦ በአቶ ኦባንግ ሜቶ የአኝዋክ ጀስቲስ ካውንስል መሪ አነሳሽነት የፊታችን ኀሙስ ተነገወዲያ ሜይ 15 ቀን 2008 እ.ኤ.አ. (ግንቦት 7 ቀን 2000 ዓ.ም.) በመላው ዓለም የሚደረገው ሰልፍ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልምም እንደሚደረግ አስተባባሪው ኮሚቴ ለኢትዮጵያ ዛሬ ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሲያትል ዶ/ር ብርሃኑ ከህዝብ ጋር ያደረጉት ውይይት

Ethiopia Zare (ሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2000 ዓ.ም. May 12, 2008)፦ ትናንት በአሜሪካን ሀገር ሲያትል ከተማ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በከተማይቱና በአቅራቢያዋ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያኖች ጋር ህዝባዊ ውይይት ባደረጉበት ወቅት "ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የሚደረግ ትግል የግድ የሚለው የትብብር ጥያቄ" በሚል ርዕስ ረዘም ያለ ንግግር አድርገዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የስደተኛውን ፓትርያርክ ዘገባ በተመለከተ አቋማችን፣ ዓላማችን እና መልሳችን

“የምናውቀውን እንናገራለን፣ ያየነውንም እንመሰክራለን”  ዮሐንስ ም. 3፥11

Ethiopia Zare (እሁድ ግንቦት 3 ቀን 2000 ዓ.ም. May 10, 2008)፦ “የማይገለጥ የተከደነ የማይታወቅም የተሰወረ ምንም የለም” ይላል በስደት የሚገኘው ህጋዊ ሲኖዶስ ዜናችንን አስተባብሎ ባወጣው መግለጫ። ሚያዚያ 24 ቀን በኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ “ስደተኛው ፓትርያርክ ለእርቅ ወደ ኢትዮጵያ ሊሄዱ ነው” በሚል ርዕስ መዘገቡ አይዘነጋም። በጉዳዩ ላይ ያገባናል የሚሉ ወገኖች በተለያዩ ድረ-ገጾች እና ራዲዮኖች የበኩላቸውን አስተያየት በመስጠት ዘገባው “ሐሰት ነው” ሲሉ አስተባብለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...