የአንድነት ፀሎት ጥሪ ለቴዲ አፍሮ

Teddy AfroEthiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 23 ቀን 2000 ዓ.ም. August 29, 2008)፦ የአርቲስት ቴዎድሮስ ካሣሁን (ቴዲ አፍሮ) አብሮ አደግ የሆኑትና የቤተልሔም ት/ቤት ተማሪዎች በየእምነታቸው በጾምና በፀሎት ሊያስቡት ማቀዳቸውን ገልጸው፣ በጾምና በፀሎቱ ለመሳተፍ ለሚፈልጉ የቴዲ አፍሮ አድናቂዎች፣ ዘመድና ወዳጆች በያሉበት በመሆን ዘር፣ ፖለቲካ፣ ኃይማኖት ወደማይለየው ፈጣሪያቸው ይማፀኑ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአ.አ. የመሬት አስተዳደር ኃላፊዎች ከ3.7 ሚሊዮን ብር በላይ በማካበታቸው ታሰሩ

Ethiopia Zare (ሰኞ ነኀሴ 19 ቀን 2000 ዓ.ም. August 25, 2008)፦ በአዲስ አበባ ከተማ ሊዝ ጽ/ቤት መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ትንሣዔ ደነቀ፣ የቦሌ ክፍለ ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር መምሪያ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ዳንኤል ስዩም እና በቦሌ ክፍለ ከተማ መሐንዲስ የሆኑት ወ/ሮ ማኅሌት አምሳሉ ከሕጋዊ ገቢያቸው ውጭ ከ3 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ በግል የባንክ አካውንታቸው ውስጥ ተገኝቷል በሚል ታሰሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አ.ሰ.አ.ድ.ድ.ማ. የአንድነት ፓርቲን ሕጋዊ ፈቃድ አስመልክቶ መግለጫ አወጣ

Ethiopia Zare (ሰኞ ነኀሴ 19 ቀን 2000 ዓ.ም. August 25, 2008)፦ ”አንድነት ሰሜን አሜሪካ የድጋፍ ድርጅቶች ማኅበር” የተሰኘውና በሰሜን አሜሪካ የሚገኘው የአንድነት ፓርቲን ሕጋዊ ፈቃድ ማግኘት ተንተርሶ ”አንድነት ፓርቲ በአዲስ ምዕራፍ ይጀመራል!” በሚል ርዕስ መግለጫ አወጣ። በዚሁ መግለጫው ላይ ማኅበሩ ለፓርቲው የሚያስፈልገውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚሰጥ ቃል ገብቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሪፖርተር ጋዜጣ ባለቤትና ዋና አዘጋጅ ከአ.አ. ጎንደር ተወስዶ ታሰረ

Amare Aregawi, Publisher & Editor-in-chief of Reporter Ethiopia Zare (ሰኞ ነኀሴ 19 ቀን 2000 ዓ.ም. August 25, 2008)፦ በሀገር ውስጥ በእንግሊዝኛ እና በአማርኛ የሚታተመው የ”ሪፖርተር” ጋዜጣ ባለቤትና ዋና አዘጋጅ አቶ አማረ አረጋዊ ዓርብ ነኀሴ 16 ቀን ከቢሮው ተወስዶ ጎንደር ውስጥ በእስር ላይ እንደሚገኝና ዛሬ ሰኞ ነኀሴ 19 ቀን ጎንደር ውስጥ ፍርድ ቤት እንደሚቀርብ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የከፍተኛ ፍርድ ቤት መዝገብ ቤት ኃላፊ በጉቦ ቅሌት ታሠሩ

‘በኢትዮጵያ ጉቦ ህጋዊ ይመስላል’ አስተያየት ሰጭዎች

Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 18 ቀን 2000 ዓ.ም. August 24, 2008)የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ክፍል፣ የመዝገብ ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ታዬ ተኮላ፣ ለልምምድ (አፓረንትሺፕ) ከመጣ ተማሪ ላይ 200 ብር ጉቦ ሲቀበሉ፣ እጅ ከፍንጅ ተይዘው የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሏቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የከፍተኛ ፍርድ ቤት መዝገብ ቤት ኃላፊ በጉቦ ቅሌት ታሠሩ

‘በኢትዮጵያ ጉቦ ህጋዊ ይመስላል’ አስተያየት ሰጭዎች

 

 

Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 18 ቀን 2000 ዓ.ም. August 24, 2008)የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ክፍል፣ የመዝገብ ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ታዬ ተኮላ፣ ለልምምድ (አፓረንትሺፕ) ከመጣ ተማሪ ላይ 200 ብር ጉቦ ሲቀበሉ፣ እጅ ከፍንጅ ተይዘው የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሏቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሦስተኛ፣ አራተኛና ሰባተኛ ወጡ

Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 18 ቀን 2000 ዓ.ም. August 24, 2008)፦ በቤጂንጉ ኦሎምፒክ ዛሬ በተደረገው የወንዶች ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሦስተኛ፣ አራተኛ እና ሰባተኛ በመውጣት ውድድሩን አጠናቀዋል። ኢትዮጵያ ሁለተኛዋን ነኀስ ለማግኘት ችላለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቀነኒሳ በቀለ ሁለተኛውን የኦሎምፒክ ክብረወሰን ሰበረ

Kenenisa Bekele, Beijing olympic, 20080823, 5000 men

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነኀሴ 17 ቀን 2000 ዓ.ም. August 23, 2008)፦ በዛሬው ዕለት በቤጂንግ ኦሎምፒክ በተካሄደው የወንዶች 5 ሺህ ሜትር የፍፃሜ ሩጫ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ለ24 ዓመታት በሞሮኮዋዊው ሰዒድ አዊታ ተይዞ የነበረውን የኦሎምፒክ ክብረወሰን በመስበር ለኢትዮጵያ አራተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል። በ10 ሺውም የኦሎምፒክ ክብረወሰንን መስበሩ አይዘነጋም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ፓርቲ ዛሬ ፈቃድ ተሰጠው

UDJ certificate
 

Ethiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 16 ቀን 2000 ዓ.ም. August 22, 2008)፦ ለወራት የፓርቲ ፈቃድ ለማግኘት ሲጠባበቅ የነበረው አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዛሬ ከምርጫ ቦርድ ፈቃዱን በእጁ ያስገባ መሆኑን የአዲስ አበባ ምንጮቻችን አስታወቁ። (ከላይ የሚመለከቱት ለአንድነት ፓርቲ ከምርጫ ቦርድ የተሰጠው ሕጋዊ የምስክር ወረቀት ነው፤ የምስክር ወረቀቱን አሳድገው ለማየት ከፈለጉ እላዩ ላይ ይጫኑት!) 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያውያንና ሶማሊያውያን ስደተኞች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ታገዱ

Ethiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 16 ቀን 2000 ዓ.ም. August 22, 2008)፦ የአሜሪካ መንግሥት ቤተሰብን ከቤተሰብ በማገናኘት ፕሮግራሙ፣ ወደ አገሩ የሚገቡ የኢትዮጵያና የሶማሊያ ስደተኞች ላይ እገዳ ጣለ። የስቴት ዲፓርትመንት ዕገዳ የተጣለባቸው በተለይ የምሥራቅ አፍሪካ ሀገሮች፣ በመጠኑ ደግሞ የላይቤሪያ ስደተኞች መሆናቸው ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...