አሜሪካ ሕወሓት እየፈጸመ ያለውን ተግባር አወገዘች

Ambassador Tibor Nagy

ሕወሓት በኤርትራ ላይ ያደረገውን ጥቃት እና በማይካድራ የፈጸመው ጭፍጨፋ በአሜሪካ ተወገዘ

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 15, 2020)፦ ሕወሓት በኤርትራ ላይ ያደረገውን ያደረሰውን የሮኬት ጥቃት፣ በማይካድራ የፈጸመውን ጭፍጨፋና በትግራይ የተፈጠረውን ችግር ዓለም አቀፍ ለማድረግ ሕወሓት የሚደረገውን ጥረት አሜሪካ እንደምታወግዝ የውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ የኾኑት አምባሳደር ቲቦር ናጊ በትዊተር ገጻቸው ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የወልቃይት ስኳር ፋብሪካ በጦር ጄት አልተደበደበም

Dr. Debratsion GebreMichael

ዶ/ር ደብረጽዮን ስኳር ፋብሪካው በጦር ጄት ተደብድቧል ያሉት ሐሰት መኾኑ ተገለጸ

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 15, 2020)፦ የጁንታው ሕወሓት መሪ ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል፤ የወልቃይት ስኳር ፋብሪካ በጦር ጄት ተደብድቧል በማለት በትናንት ምሽት የሰጡት መግለጫ ሐሰት መኾኑ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ዘግናኝ ጥቃት መፈጸሙን ኮሚሽኑ አስታወቀ

ቤንሻንጉል ጉሙዝ

ጥቃቱ የተፈጸመው እየተጓዘ ባለ አውቶቡስ ላይ ነው
በጥቃቱ እስካሁን 34 ንጹኀን ዜጎች ተጎጂ ኾነዋል

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 15, 2020)፦ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመጓዝ ላይ ባለ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ላይ ዘግናኝ ነው ባለው ጥቃት ጉዳይ እንደደረሰ አመለከተ። እስካሁን በደረሰው መረጃ በዚህ ጥቃት 34 ሰዎች እንደተጎዱና ይህ ቁጥር እንደሚጨምር የሚጠበቅ መኾኑን፤ “ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጸጥታና ደኅንነት ለማጠናከር ፈጣንና የተቀናጀ እርምጃ አስፈላጊ ነው” በሚል ርዕስ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጽንፈኛው ቡድን ላይ የሚወሰደውን እርምጃ ዓለም ሊደግፈው እንደሚገባ ተገለጸ

Getachew Reda

“ጁንታው ቡድን የፈጸማቸውን ወንጀሎች አቶ ጌታቸው ረዳ አምነዋል”

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 15, 2020)፦ ጽንፈኛውን የሕወሕት ቡድን ለሕግ ለማቅረብ እየተወሰደ ያለውን እርምጃ ዓለም አቀፉ ሕብረተሰብ ሊደግፈው እንደሚገባና ጽንፈኛው ቡድን በንጹኀን ላይ እያደረሰ ያለውን የግፍ ተግባር ሊያወግዙት እንደሚገባ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቻይናውያን የአገራቸውን ባንዲራ እያውለበለቡ ከትግራይ እየወጡ ነው

Chinese are leaving from Tigray region

ዶ/ር ዐቢይ ለትግራይ ክልል ልዩ ኃይል እጁን እንዲሰጥ የሰጡት 72 ሰዓት እያለቀ ነው

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 15, 2020)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል እጁን እንዲሰጥ የተሰጠው የ72 ሰዓታት ከመጠናቀቁ በፊት በትግራይ ውስጥ የሚገኙ ቻይናውያን ከመቀሌና ከተለያዩ የክልሉ ከተሞች መውጣት ጀምረዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ ብቻዋን ሕግ የማስከበር ዘመቻውን በብቃት እንደምታጠናቅቅ ዶ/ር ዐቢይ ገለጹ

PM Abiy Ahmed

የሕግ የበላይነትን የማስከበር ሥራ በጥሩ ሁኔታ እየሔደ ነው አሉ

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 15, 2020)፦ በትግራይ ክልል የሚካሔደው የሕግ የበላይነትን የማስከበር ሥራ በጥሩ ሁኔት እየተካሔደ መኾኑንና ኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት የማስከበሩን ዘመቻ በብቃት እንደሚጠናቀቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጥፋት ተልዕኮ የተጠረጠሩ 18 ግለሰቦች ድሬ ዳዋ ላይ ተያዙ

Dire Dawa

ከጁንታው የሕወሓት ቡድን ጋር ግንኙነት አላቸው

ኢዛ (ቅዳሜ ኅዳር ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 14, 2020)፦ የድሬ ዳዋ ፖሊስ በድሬ ዳዋ የጥፋት ተልዕኮ እንዳላቸው የተጠረጠሩ 18 ግለሰቦችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ። ግለሰቦቹ ከሕወሓት ጁንታ ቡድን ጋር ግንኙነት እንዳላቸው አክሎ ገልጿል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በምንም ምክንያት ርችት መተኮስ ተከለከለ

Fireworks banned in Addis Ababa

ርችት የሚተኮስ ግለሰብም ኾነ ተቋም በሕግ ይጠየቃል

ኢዛ (ቅዳሜ ኅዳር ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 14, 2020)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ በምንም ሁኔታ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ርችት እንዳይተኮስና ርችት የተኮሰ ግለሰብም ኾነ ተቋም በሕግ የሚጠየቅ መኾኑን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ የሚደረጉ በረራዎች ተሰረዙ

Gonder Airport

ምክንያቱ በባሕር ዳር እና በጎንደር የተከሰተውን የሮኬት ጥቃት ነው

ኢዛ (ቅዳሜ ኅዳር ፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 14, 2020)፦ በባሕር ዳር እና በጎንደር የተከሰቱትን ፍንዳታዎች ተከትሎ ጥቃቱ በደረሰ ማግስት ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ይደረጉ የነበሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራዎች እንዲሰረዙ ተደርገዋል። የሮኬት ጥቃቱ የፈጸመው የሕወሓት ጁንታ ቡድን ትናንት ከምሽቱ አምስት ሰዓት ላይ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ