ወደ ባሕር ዳርና መቀሌ በረራ ተቋረጠ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የኢትዮጵያ አየር መንገድንም ይጨምራል

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፳፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 4, 2020)፦ ወደ ባሕር ዳር እና ወደ መቀሌ የሚደረጉ የአየር በረራዎች ሙሉ ለሙሉ መቆማቸው ታውቋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጨምሮ ሁሉም በረራዎች ናቸው የተቋረጡት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሕወሓት በደንሻ በኩል ጦርነት ከፍቷል

TPLF

በዳንሻሕና በሌሎች ሁለት አካባቢዎች ሕወሓት ሊያደርስ የነበረው ጥቃት መክሸፉን አቶ ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፳፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 4, 2020)፦ በትግራይ ክልል ውስጥ በሚገኘው የአገር መከላከያ ካምፕ ላይ ሕወሓት ጥቃት ማድረሱንና በዳንሻሕ በኩል ጦርነት መክፈቱ ተገለጸ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የቀዩ መስመር የመጨረሻው ነጥብ አልፏል አሉ። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በደንሻና በሌሎች ሁለት አካባቢዎች ሕወሓት ሊያደርስ የነበረው ጥቃት መክሸፉን ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሕወሓት ትግራይ ውስጥ ያለውን የሰሜን ዕዝ እንዳጠቃና የዘረፋ ሙከራ እንዳደረገ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ

PM Abiy Ahmed

"የመከላከያ ሠራዊቱ በኮማንድ ፖስት እየተመራ አገሩን የማዳን ተልዕኮ ተሰጥቶታል" ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ

ኢዛ (ማክሰኞ ጥቅምት ፳፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 3, 2020)፦ ሕወሓት ትግራይ ውስጥ የሚገኘውን የሰሜን ዕዝ የመከላከያ ካምፕ ማጥቃቱንና የዘረፋ ሙከራ ማድረጉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ሌሊት አስታውቁ። የመከላከያ ሠራዊቱ በኮማንድ ፖስት እየተመራ አገሩን የማዳን ተልዕኮ ተሰጥቶታል ብለዋለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥትና መከላከያ የታሉ?

ፓርላማው በእንባ ሲራጭ ዋለ

ፓርላማው የጀገነበት የፓርላማ ውሎ

ኢዛ (ማክሰኞ ጥቅምት ፳፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 3, 2020)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በዛሬው ዕለት ያካሔዱት ስብሰባ በተለየ መልኩ የተካሔደ ነበር። በጥቁር የኀዘን ልብስና በእንባ ጭምር የታጀበው የዛሬው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ፤ በዕለቱ ለውይይት ተይዞ የነበረውን አጀንዳ በመተው መወያየት የምንፈልገው በወቅታዊ የአገራችን ጉዳይ ነው በማለት የጀገኑበት ነበር ማለት ይቻላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነጃዋር መሐመድ ለድኅንነታችን እንሰጋለን በማለት ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀሩ

Jawar Mohammed (L), Bekele Gerba (R)

“አሁን ባለው ሁኔታ በእነርሱ ላይ ጥቃት ቢፈጸም አገሪቷ የባሰ ችግር ውስጥ ትግባለች በማለት ነው ፍርድ ቤት ያልቀረቡት” አቶ ሃምዛ

ኢዛ (ማክሰኞ ጥቅምት ፳፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 3, 2020)፦ አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባ ዛሬ ማክሰኞ ጥቅምት 23 ቀን 2013 ዓ.ም. ፍርድ ቤት በነበራቸው ቀጠሮ ላይ ለደኅንነታችን እንሰጋለን በማለት ችሎት ሳይቀርቡ መቅረታቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በምዕራብ ወለጋ ማንነትን መሠረት ባደረገ ጥቃት ከ200 በላይ ሰዎች መሞታቸው እየተነገረ ነው

የአብን ዓርማ (ግራ)፣ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ (መኻል)፣ አቶ መላኩ አለበል (ቀኝ)

“በአማራ ሕዝብ ላይ በየቦታው እየተፈጸመ ላለው የዘር ማጥፉት ወንጀል ሙሉ ኃላፊነቱን መንግሥት ይወስዳል” አብን
“የአማራን ሕዝብ ማኅበራዊ እረፍት በመንሳት የራስን ሰላም ማግኘት አይቻልም!” የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት

ኢዛ (ሰኞ ጥቅምት ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 2, 2020)፦ በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ጋንቃ ቀበሌ ትናንት በኦነግ ሸኔ በተፈጸመው የሽብር ጥቃት ሕይወታቸው ያለፉ ዜጎች ስብሰባ በተጠሩበት ስፍራ ቦምብ ተወርውሮባቸው የተገደሉ ስለመኾኑ ተገለጸ። በዚህ ማንነትን መሠረት ባደረገ ግድያ ከ200 በላይ አማሮች እንደተገደሉ ተነግሯል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በምዕራብ ወለጋ የጸጥታ ኃይሉ በኦነግ ሸኔ ላይ እርምጃ እየወሰደ መኾኑ ተገለጸ

Shimelis Abdisa

በዚህ አካባቢ በተፈጠረው የኦነግ ሸኔ ጥቃት ጉዳት ደርሷል
“በኦነግ ሸኔና በወያኔ የጥፋትና የሽብር ሴራ ኢትዮጵያ አትፈርስም” የኦሮሚያ ፕሬዝዳንት

ኢዛ (ሰኞ ጥቅምት ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 2, 2020)፦ በትናንትናው ዕለት (እሁድ ጥቅምት 21 ቀን 2013 ዓ.ም.) በምዕራብ ወለጋ ዞን ጉሊሶ ወረዳ ጋዋ ጋንቃ በተባለው ቀበሌ ኦነግ ሸኔ የሽብር ጥቃት መፈጸሙንና በአሁኑ ወቅትም በአካባቢው የመከላከያ ሠራዊት እርምጃ እየወሰደ መኾኑን ተከትሎ፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ፤ “በኦነግ ሸኔና በወያኔ የጥፋትና የሽብር ሴራ ኢትዮጵያ አትፈርስም” ብለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኃኖም በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ራሳቸውን አገለሉ

Dr. Tedros Adhanom

ከአንድ በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ተገናኝተው ነበር

ኢዛ (ሰኞ ጥቅምት ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 2, 2020)፦ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድኃኖም በኮሮና ቫይረስ ከተያዘ አንድ ግለሰብ ጋር መገናኘታቸውን በማስታወቅ፤ ራሳቸውን ማግለላቸውን ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. በትዊተር ገጻቸው አሳወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኤርትራ መንግሥት ሕወሓትን የሚወነጅል መግለጫ አወጣ

President Isaias Afwerki (L), Debretsion Gebremichael (PHD)

“ወያኔ በሞት ጣር ላይ ኾኖ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ግን፤ በአካባቢው የተፈጠረውን ሁኔታ ወደ ኋላ ሊመልሰው አይችልም” የኤርትራ መንግሥት

ኢዛ (ቅዳሜ ጥቅምት ፳፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 31, 2020)፦ በምሥራቅ አፍሪካ መታየት የጀመረውን ለውጥ ትግራይ ተቋዳሽ እንዳትኾን ሕወሓት እንቅፋት ኾኗል ሲል የኤርትራ መንግሥት አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫው በግንቦት መጨረሻ ወይም በሰኔ መጀመሪያ ላይ ይካሔዳል

National Election Board of Ethiopia (NEBE)

ትክክለኛውን ቀን ወደፊት ያሳውቃል ተብሎ ይጠበቃል

ኢዛ (ዓርብ ጥቅምት ፳ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 30, 2020)፦ ባለፈው ዓመት 2012፣ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የተሸጋገረው ስድስተኛው አገር አቀፍ ምርጫ በያዝነው ዓመት 2013 ዓ.ም. ከግንቦት አጋማሽ እስከ ሰኔ አጋማሽ ድረስ ባሉት ሳምንታት ውስጥ ለማካሔድ ውጥን መያዙን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ