በአቶ ልደቱ አያሌው ጉዳይ ተለዋጭ ቀጠሮዎች ተሰጡ

Lidetu Ayalew

የጤና ሁኔታቸው አስጊ ደረጃ ላይ መኾኑን በማመልከት ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ መርምሮ ትእዛዝ ለመስጠት ለኅዳር 18 ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ

ኢዛ (ሐሙስ ጥቅምት ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 5, 2020)፦ አቶ ልደቱ አያሌው ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት በተከሰሱበት ወንጀል መከላከያ ማስረጃ እንዲያቀርቡ የኦሮሚያ ክልል የምሥራቅ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ብይን ሰጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሰብአዊ መብት ኮምሽን የትግራይ የጸጥታ ሁኔታ ያሳስበኛል አለ

Danile Bekele (PHD), Ethiopian Human Rights Commission

የሲቪል ሰዎች ደኅንነት መረጋገጥ ይኖርበታል ብሏል

ኢዛ (ሐሙስ ጥቅምት ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 5, 2020)፦ ከወቅታዊው ጉዳይ ጋር በተያያዘ በትግራይ ክልል የሲቪል ሰዎችን ደኅንነት እና የሰብአዊ እርዳታ አገልግሎት አቅርቦት ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ እና እየተባባሰ የቆየውን የትግራይ ክልል የጸጥታ ሁኔታ የሚያሳስበው መኾኑን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮምሽን (ኢሰመኮ) ዛሬ ሐሙስ ጥቅምት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የጸጥታ ኃይሉ ትጥቅ እንዲፈታ ጭምር የሚያስገድድ ነው

ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ

ግብረ ኃይሉ እንዳስፈላጊነቱ ማንኛውም የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ወደ ትግራይ ክልል እንዳይገባም ኾነ እንዳይወጣ ትእዛዝ መስጠት ይችላል

ኢዛ (ሐሙስ ጥቅምት ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 5, 2020)፦ አዋጁ ተፈጻሚ በሚኾንበት ክልል ውስጥ ፖሊስ ወይንም ሌላ ማንኛውም የጸጥታ ኃይል ትጥቁን እንዲፈታ ትእዛዝ መስጠት የሚችል መኾኑ ተገለጸ። በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ዙሪያ ዛሬ ሐሙስ ጥቅምት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ፤ ግብረ ኃይሉ አካባቢውን ለመቆጣጠርና ሰላምን ለማስፈን አስፈላጊውን እርምጃ የመውሰድ ሥልጣንም እንደተሰጠው ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ኢትዮጵያውያን ከመከላከያ ጐን እንዲኾኑ ጥሪ አቀረበ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት

በመከላከያ ሠራዊቱ ላይ አሳዛኝና አሳፋሪ ጥቃት ተፈጽሟል ብሏል

ኢዛ (ሐሙስ ጥቅምት ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 5, 2020)፦ ከትናንት በስቲያ ምሽት ላይ በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ የተለያዩ ተቋማት ድርጊቱን በማውገዝ አቋማቸውን እያስታወቁ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለትም የፌዴሬሽን ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ከመከላከያ ሠራዊት ጎን በመቆም ተገቢውን ድጋፍ ሊያደርጉ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በትግራይ ክልል ለታወጀው አስቸኳይ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ተሰየመ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

ቦርዱ ሰባት አባላት አሉት

ኢዛ (ሐሙስ ጥቅምት ፳፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 5, 2020)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ሐሙስ ጥቅምት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. ባካሔደው በመደበኛ ስብሰባው የሚኒስትሮች ምክር ቤት በትግራይ ክልል ያወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማጽደቅ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም መርማሪ ቦርድ አባላትን ሰየመ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቀንሰው የነበሩ ሦስት ጄኔራሎች ወደ ሠራዊቱ እንዲመለሱ አዘዙ

ጄኔራሎች ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ እና ሌ/ጄ አበባው ታደሰ

ሦስቱ ጄኔራሎች ሌ/ጄኔራል ባጫ ደበሌ፣ ሌ/ጄ ዮሐንስ ገብረመስቀል እና ሌ/ጄ አበባው ታደሰ ናቸው

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 4, 2020)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአገር መከላከያ ሠራዊት ተቀንሰው የነበሩትን ሦስት ጄኔራሎች ወደ መከላከያ ሠራዊት እንዲመለሱ ትእዛዝ ሰጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሱዳንና ኢትዮጵያ በድንበር ላይ የተጠናከረ ጥበቃ ለማድረግ ተስማሙ

PM Abiy Ahmed (L) and Abdel Fattah Al-burhan (R)

ሱዳን ድንበርዋን ዘግታለች

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 4, 2020)፦ ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስናት ድንበር ላይ ጠንካራ የጋራ የጸጥታ ለማካሔድ ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ጋር መስማማታቸውን የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥት ለትግራይ ክልል ልዩ ኃይል ጥሪ አቀረበ

TPLF

ሙሉና አስተማማኝ ዋስትና እሰጣለሁ ብሏል

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 4, 2020)፦ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መንግሥት አሁን ባወጣው መግለጫ፤ ተገድደውና ሳይፈልጉ ወደ ጦርነት የገቡ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል አባላት በሰላማዊ መንገድ ወደ አጎራባች ክልሎችና በአቅራቢያቸው ወደአለው የመከላከያ ሠራዊት ከገቡ ሙሉና አስተማማኝ ዋስትና እንደሚሰጣቸው አስታወቀ። (ኢዛ)

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በትግራይ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ደነገገ

PM Abiy Ahmed

የጦር ኃይሎች ኤታማዦር ሹሙ አዋጁን የሚያስፈጽም ሲሆን፤ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ይኾናል

ኢዛ (ረቡዕ ጥቅምት ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 4, 2020)፦ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ረቡዕ ጥቅምት 25 ቀን 2013 ዓ.ም. ባካሔደው ልዩ ስብሰባ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ