የ2013 ዓ.ም. 1ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 1st, 2013 Ethiopian calendar

 

የዓመቱ አንደኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከመስከረም 4 - 10 ቀን 2013 ዓ.ም.) ያሳለፍነው ሳምንት መሪ ዜና ኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘብዋ የኾነውን የብር ኖት ለውጥ ማድረጓ ነው። ከዚህ ዜና ባሻገር ከሳምንቱ አነጋጋሪና ትኩረት ሳቢ ዜናዎች ውስጥ የጤና ሚኒስትሯ ቀጣዩን ምርጫ በጥንቃቄ ማድረግ ይቻላል የሚል ሪፖርት ለፓርላማ ማቅረባቸው ተጠቃሽ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሀንፈሬ አሊሚራህ አረፉ

ሀንፈሬ አሊሚራህ

“እንኳን እኛ ግመሎቻችን የኢትዮጵያን ባንዲራ ይለዩታል” ሀንፈሬ አሊሚራህ

ኢዛ (እሁድ መስከረም ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 20, 2020)፦ የአፋር ሱልጣን ሀንፈሬ አሊሚራህ ባደረባቸው ሕመም የሕክመና ክትትል ሲያደርጉ ቆይተው፤ በ74 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ባንኮች የባለቤትነት ጥያቄ ያልቀረበበትን ገንዘብ ለብሔራዊ ባንክ አስገቡ ተባሉ

National Bank of Ethiopia

ከ18ቱ ባንኮች ድንጋጌው የሚመለከታቸው አሥሩን ብቻ ነው

ኢዛ (እሁድ መስከረም ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 20, 2020)፦ በሁሉም የአገሪቱ ንግድ ባንኮች ውስጥ በደንበኞቻቸው ተከፍተው ለ15 እና ከዚያ በላይ ዓመታት የባለቤትነት ጥያቄ ሳይቀርብባቸው የቆዩ ተከፋይ ሒሳቦችን፣ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንዲያስገቡ የሚደነግግ ሕግ መውጣቱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከል ተመረቀ

Ethiopian Artificial Intelligence Center

ማዕከሉ ከመመረቁ በፊት በጡት ካንሠርና የጭንቅላት ዕጢ ላይ ሲሠራ ነበር

ኢዛ (እሁድ መስከረም ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 20, 2020)፦ ሰው ሠራሽ የኾነ የማሰብ ክህሎትን በተለያዩ የሥራ መስኮች የሚያሰማራ ቴክኖሎጂን የሚያሰርጸው የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ማዕከል ዛሬ እሁድ መስከረም 10 ቀን 2013 ዓ.ም. ተመርቆ አገልግሎት ጀመረ። በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ሐሳብ አመንጪነት የተገነባው ይህ ማዕከል፤ ሙሉ ለሙሉ ራሳቸውን ችለው ለሰው ልጅ አድካሚ የኾኑ ተግባራትን በፍጥነት ማከናወን የሚያስችሉ ማሽኖችን የያዘ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እነአቶ ጃዋር መሐመድ በተደራራቢ ወንጀሎች ክስ እንደተመሠረተባቸው ተገለጸ

Jawar Mohammed (L), Bekele Gerba (M) and Federal Attorney General

የፊታችን ሰኞ መስከረም 11 ቀን ክሱ ይደርሳቸዋል

ኢዛ (ቅዳሜ መስከረም ፱ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 19, 2020)፦ እነአቶ ጃዋር መሐመድ የሽብር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅና ሌሎች አዋጆችን በመተላለፍ በፈጸሙት ወንጀል ተደራራቢ ክሶች እንደተከፈተባቸው ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጥንቃቄ ምርጫውን ማካሔድ እንደሚቻል ጤና ሚኒስትሯ ገለጹ

የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ (በግራ)፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ምርጫ ቦርድና ኮሮና ቫይረስ

ፓርላማው ጉዳዩ ወደሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 18, 2020)፦ ዛሬ ዓርብ መስከረም 8 ቀን 2013 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመገኘት ቀጣዩን አገራዊ ምርጫ በተመለከተ አጭር ሪፖርት ያቀረቡት የጤና ሚኒስትሯ፤ የኮሮና ቫይረስ ሥርጭት ተንተርሶ ተገቢውን ጥንቃቄና አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ ምርጫ ማካሔድ የሚቻል ስለመኾኑ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ልደቱ በተከሰሱበት ክስ መቃወሚያቸውን አቅረቡ

Lidetu Ayalew

የዋስትና ጥያቄው በሕይወት መኖርና ያለመኖር ነው አሉ

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 18, 2020)፦ አቶ ልደቱ አያሌው ትናንት በተመሠረተባቸው የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት ክስ ላይ መቃወሚያቸውን አቀረቡ። ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ትእዛዝ ለመስጠት ለመስከረም 12 ቀን 2013 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 53ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 53rd, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ ሃምሳ ሦስተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከጳጉሜን 1 ቀን 2012 ዓ.ም. - መስከረም 3 ቀን 2013 ዓ.ም.) እንኳን ለ2013 አዲስ ዓመት አደረሰን! አዲሱ ዓመት የሰላም የእድገትና የብልጽግና ይሆን ዘንድ እንመኛለን! ያሳለፍነው ሳምንት የ2012 ዓ.ም. የመጨረሻ ቀናት የአዲሱ ዓመት የመጀመሪያዎቹ ሦስት ቀናት ያረፉበት ነው። በእነዚህ ያሳለፍናቸው ሰባት ቀናት በኢትዮጵያ ከተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች መካከል አዲሱን ዓመት አስታክኮ የአዲስ አበባን ገጽታ በተለየ መልኩ የቀየረው የሸገር ፓርክ ምርቃት በወታደራዊ ትርዒት ታጅቦ በይፋ መመረቁ አንዱ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በብር ኖት ለውጡ ምክንያት ንብረት በጥሬ ገንዘብ መገበያየት ተከለከለ

Ethiopian Birr notes

በስጦታ የሚተላለፉ ውሎች አገልግሎት ቆሟል

ኢዛ (ሐሙስ መስከረም ፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 17, 2020)፦ ማንኛውም ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀስ ንብረት በጥሬ ገንዘብ መግዛት የሚከለክለውን አሠራር ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ