አቶ ልደቱ ያልተፈቀደ የጦር መሣሪያ በመያዝ ወንጀል ተከሰሱ

Lidetu Ayalew (Photo: Addis Fortune)

ላቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ነገ ውሳኔ ይሰጣል

ኢዛ (ሐሙስ መስከረም ፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 17, 2020)፦ የዋስትና ጥያቄያቸው ተቀባይነት ያጣውና በእስር ላይ የሚገኙት አቶ ልደቱ አያሌው ያልተፈቀደ የጦር መሣሪያ በመያዝ ወንጀል ክስ ቀረበባቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከኃላፊነታቸው ተነሱ

Prof. Kindeya GebreHiwot

ከኃላፊነታቸው የተነሱበት ምክንያት አልተገለጸም

ኢዛ (ሰኞ መስከረም ፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 14, 2020)፦ ከግንቦት 28 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ የመቀሌ ዩኒቨርሲቲን በፕሬዝዳንትነት ሲመሩ የቆዩት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ከኃላፊነታቸው ተነሱ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ የብር ኖቶች ተቀየሩ

The new Ethiopian Birr

ለመጀመሪያ ጊዜ የ200 ብር ኖት ወጥቷል

(ኢዛ ሰኞ ፬ መስከረም ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 14, 2020)፦ የኢትዮጵያ መገበያያ ገንዘብ የብር ኖቶች ስለመቀየራቸው በይፋ ተነገረ። ሁሉም የብር ኖቶች ከዛሬ ጀምሮ መቀየሩን ይፋ ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኦነግ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዳውድ ኢብሳን ከፓርቲው አገደ

Dawud Ibas and OLF leaders

አዲስ ምርጫ እስኪካሔድ ምክትላቸው ተተክተዋል

ኢዛ (እሁድ መስከረም ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 13, 2020)፦ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ሥራ አስፈጻሚ የድርጅቱን ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳን ከሊቀመንበርነታቸውና ከፓርቲው እንዲታገዱ ውሳኔ ማሳለፉ ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አወዛጋቢው የትግራይ ምርጫ ውጤት ተብሎ የተገለጸው የሕወሓትን 98 በመቶ አሸናፊነት ያሳያል ተባለ

TPLF

ተቃዋሚዎቹ 20 በመቶ ወንበር በችሮታ ይሰጣቸዋል

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 11, 2020)፦ በፌዴሬሽን ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ተቀባይነት የሌለውና እንዳልተደረገ ይቆጠራል የሚል ውሳኔ በተላለፈበት የትግራይ ክልል ምርጫ 2012፤ ሕወሓት 98.2 በመቶውን ድምፅ አግኝቶ አሸነፈ ተባለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮ ቴሌኮም ሽያጭ ቁርጥ ኾኗል

Ethio Telecom

40 በመቶ ለውጭ ኩባንያዎች ይሸጣል
መንግሥት 55 በመቶውን ድርሻ ይይዛል
ለኢትዮጵያውያኖች አምስት በመቶ ድርሻ ይሸጣል

ኢዛ (ሰኞ ጳጉሜን ፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 7, 2020)፦ በኢትዮጵያ በመንግሥት ይዞታ ሥር ከሚገኙ ግዙፍ ኩባንያዎች ውስጥ አንዱ የኾነው ኢትዮ ቴሌኮም በከፊል ለውጭ ኩባንያዎች ለመሸጥ የተጀመረው እንቅስቃሴ በአንዳንድ ወገኖች ጥያቄ እያስነሳ ቢኾንም፤ የኩባንያው 40 በመቶ ድርሻ ለውጭ ኩባንያዎች እንዲተላለፍ ውሳኔ ላይ ስለመደረሱ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዓቃቤ ሕግ በእነአቶ ጃዋር መሐመድ ላይ በ14 ቀን ክስ እንዲመሠርት ብይን ተሰጠ

Jawar Mohammed (L), Bekele Gerba (M) and Hachalu Hundessa (R)

በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ እና በእነ አቶ እስክንድር ላይ እስከ ጳጉሜን 5 ድረስ ክስ እንደሚመሠርት ዓቃቤ ሕግ አስታወቀ

ኢዛ (ሰኞ ጳጉሜን ፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 7, 2020)፦ አቶ ጃዋር መሐመድና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ አስር ተጠርጣሪዎች ላይ ዓቃቤ ሕግ እስከ መስከረም 8 ቀን 2013 ዓ.ም. ድረስ ክስ እንዲመሠርት ጉዳዩን የያዘው ፍርድ ቤት በዛሬው ዕለት (ሰኞ ጳጉሜን 2 ቀን 2012 ዓ.ም.) ብይን ሰጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአስራት ቴሌቭዥን የሚዲያ ባለሙያዎች በዋስ እንዲወጡ ቢፈቀድም አልተለቀቁም

Asrat

መርማሪ ፖሊስ ለፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ይግባኝ በማለቱ በእስር እንዲቆዩ ተደርጓል

ኢዛ (ሰኞ ጳጉሜን ፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 7, 2020)፦ በሚዲያ ኹከትን ቀስቅሰዋል ተብለው በእስር ላይ የነበሩት የአስራት ቴሌቪዥን የሚዲያ ባለሙያዎች እና የካሜራ ባለሙያዎች የዋስትና ተፈቅዶላቸው እንዲፈቱ ፍርድ ቤት ቢፈቅድም፤ ከእስር አልተለቀቁም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 52ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 52nd, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ ሃምሳ ሁለተኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከነኀሴ 25 - ጳጉሜን 1 ቀን 2012 ዓ.ም.) ባሳለፍነው ሳምንት ዐበይት አገራዊ ጉዳይ ኾኖ የሚጠቀሰው የፌዴሬሽን ምክር ቤት የትግራይ ክልል አደርገዋለሁ ያለው ምርጫ የማይጸና ስለመኾኑ የመጨረሻ ውሳኔ ማሳለፉ ነው። የብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሥልጠና መጠናቀቂያ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ሌብነት የብልጽግና ጉዞ ካንሰር መኾኑን የገለጹት በዚሁ ባሳለፍነው ሳምንት ነው። አንታገስም ማለታቸውን ያደመጥንበትም ሳምንት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ