የትግራይ ክልል አካሒደዋለሁ ያለው ምርጫ ኢ-ሕገ መንግሥታዊ ነው ተባለ
ምርጫው ቢደረግ፤ የማይጸና መኾኑንም የፌዴሬሽን ምክር ቤት ወሰነ
ኢዛ (ቅዳሜ ነኀሴ ፴ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 5, 2020)፦ የትግራይ ክልል አካሒደዋለሁ ያለው ምርጫ ኢ-ሕገ መንግሥታዊ መኾኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ አሳለፈ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ቅዳሜ ነኀሴ ፴ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 5, 2020)፦ የትግራይ ክልል አካሒደዋለሁ ያለው ምርጫ ኢ-ሕገ መንግሥታዊ መኾኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ አሳለፈ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ዓርብ ነኀሴ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 4, 2020)፦ አቶ ልደቱ አያሌው በሌላ መዝገብ በቀረበባቸው ክስ ለቢሾፍቱ (ለደብረዘይት) ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደርገባቸው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ዓርብ ነኀሴ ፳፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 4, 2020)፦ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ነገ የጠራው አስቸኳይ ስበሰባ አጀንዳ ቀድሞ ካልደረሰው፤ ክልሉን የሚወክሉ አባላት በስብሰባው ላይ እንደማይሳተፉ የትግራይ ክልል ምክር ቤት ገለጸ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ ነኀሴ ፳፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 1, 2020)፦ ትናንት ረፋድ ላይ ጀምሮ የብዙዎችን ዓይንና ጆሮ የያዘው በአዲስ አበባ ተፈጸመ ስለተባለው ሕገወጥ የመሬት ወረራና ያልተገባ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እደላን ለተመለከተው የኢዜማ መረጃ በቀጥታም ኾነ በተዘዋዋሪ ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ተብለው የሚታመኑት የቀድሞው የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጂንየር ታከለ ኡማ፤ የኢዜማን መግለጫ በመኮነን ድምፃቸውን አሰሙ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ ነኀሴ ፳፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 1, 2020)፦ የቀድሞው የጦር መኮንንና የኦሮሞ ብሔራዊ ፓርቲ መሥራችና ሊቀመንበር ብርጋዲየር ጄኔራል ከማል ገልቹ ፓርቲያቸውን አክስመው የብልጽግና ፓርቲን ተቀላቀሉ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሰኞ ነኀሴ ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 31, 2020)፦ በአቶ ልደቱ አያሌው ላይ ክስ እስኪመሠረት ተጨማሪ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው የጠየቀው መርማሪ ፖሊስ፤ ጥያቄውን ፍርድ ቤቱ ውድቅ በማድረግ፤ አቶ ልደቱ በሌላ መዝገብ የዋስትና ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ ትእዛዝ ተሰጠ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሰኞ ነኀሴ ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 31, 2020)፦ ኢዜማ በአዲስ አበባ ከ213,000 ካሬ ሜትር በላይ መሬት በሕገወጥ መንገድ መታደሉንና 95 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሕገወጥ መንገድ ለማይመለከታቸውና ለጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ላልቆጠቡ ሰዎች መተላለፉን የሚያመለክተውን በጥናት ላይ የተደገፈ ሪፖርቱን ዛሬ ሰኞ ነኀሴ 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል። ጥናቱ የተጠናው በአዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኙት አሥር ክፍለ ከተሞች ውስጥ በአምስቱ ክፍለ ከተሞች በተመረጡ 25 ቦታዎች ላይ ብቻ ነው። በዚህ ወንጀል እጃቸው ያለበት ባለሥልጣናት ለፍርድ ይቅረቡ ብሏል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ከነኀሴ 18 - 24 ቀን 2012 ዓ.ም.) ባሳለፍነው ሳምንት ውስጥ አነጋጋሪ ከነበሩ ዜናዎች መካከል ኢዜማ ከመሬት ወረራና ከኮንዶሚኒየም አሰጣጥ ጋር ተያይዞ ሊሰጥ የነበረው መግለጫ መከልከሉ ነው። አዲሷ ምክትል ከንቲባ ሳምንቱን በተለያዩ ክንውኖች የዜና ሽፋን የተሰጣቸው ሲሆን፤ ጐልቶ የሚጠቀስላቸው ደግሞ የከተማዋን የሰላም ምክር ቤት በይፋ ማቋቋማቸው ነው። ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. በመስቀል አደባባይ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ግድያ ለመፈጸም ቦምብ በመወርወር ተጠርጥረው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት ሲታይ የነበሩት አምስት ተከሳሾች፤ ጥፋተኛ መባላቸው የተሰማው በዚህ ሳምንት ነበር። ፍርዳቸው ጥቅምት 17 ቀን 2013 ዓ.ም. ይጠበቃል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ዓርብ ነኀሴ ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 28, 2020)፦ ኢዜማ በአዲስ አበባ ከተማ ያለውን የመሬት ወረራና የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ኢፍትሐዊ ዕደላን በተመለከተ ሲያዘጋጀው የነበረው ጥናት ላይ የቀድሞው የከተማዋ ከንቲባ ታከለ ኡማ ጽሕፈት ቤት፤ የመሬት ልማት ቢሮና የቤቶች ኤጀንሲን ምላሽ ለማካተት ጥያቄ አቅርቦ ምላሽ ቢያጣም፤ በዛሬው ዕለት በጉዳዩ ላይ ሊሰጥ የነበረው መግለጫ በፖሊስ ታገደ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ዓርብ ነኀሴ ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 28, 2020)፦ በቅርቡ ከወላይታ ዞን አስተዳዳሪነታቸው በተነሱት በአቶ ዳጋቶ ኩምቤ ምትክ፤ ዶ/ር እንድሪያስ ጌታ እንደተሾሙ ተገለጸ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...