በሁለት ቀናት 513 የቫይረሱ ተጠቂዎች ተገኝተዋል

Total coronavirus cases in Ethiopia, June 13, 2020

የሟቾች ቁጥር ወደ 55 ከፍ ብሏል

ኢዛ (ቅዳሜ ሰኔ ፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 13, 2020)፦ በኢትዮጵያ አድማሱን እያሰፋ ያለው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ባለፉት ሁለት ቀናት ብቻ በ513 ሰዎች ላይ መገኘቱንና አጠቃላይ በአገሪቱ በወረርሽኙ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 3,166 ደረሰ። የሟቾች ቁጥርም እየጨመረ በመምጣቱ 55 ኾኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የትግራይ ክልል ምክር ቤት ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ በተፃራሪ በክልሉ ምርጫ ለማድረግ ወሰነ

TPLF and Ethiopian Election 2020

ውሳኔውን ያጸደቀው በሙሉ ድምፅ ነው

ኢዛ (ዓርብ ሰኔ ፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 12, 2020)፦ የትግራይ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛውን ክልላዊ ምርጫ፤ በክልል ደረጃ ለማካሔድ በሙሉ ድምፅ ማጽደቁ ተሰማ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ወሰነ

House of Peoples’ Representatives of the Federal Democratic Republic of Ethiopia

ምርጫውን ለማራዘም የቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ አጸደቀ
የውሳኔ ሐሳቡ የጸደቀው በ114 ድጋፍና በአራት ተቃውሞ ነው

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 10, 2020)፦ የፌዴሬሽን ምክር ቤት የኮሮና ወረርሽኝ የአገሪቱ ሥጋት ኾኖ እስከቀጠለ ድረስ፤ ሁሉም የፌዴራልና የክልል ምክር ቤቶች ሥራቸውን እንዲቀጥሉና ስድስተኛው ምርጫም ወረርሽኙ ሥጋት አለመኾኑ ከተረጋገጠ በኋላ ከዘጠኝ ወር እስከ አንድ ዓመት ባለው ጊዜ እንዲካሔድ አጸደቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ብሔራዊ ሙዚየም 200 ሺህ ጎብኝዎችና ከነርሱ ሊያገኝ የሚችለውን ገቢ አጣ

Nationa Museum of Ethiopia

ከመጋቢት 8 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ተዘግቷል

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 10, 2020)፦ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ከተቀሰቀሰ ወዲህ ቀድመው አገልግሎት ማቋረጣቸውን ካስታወቁት የቱሪዝም መዳረሻ ተቋማት መካከል አንዱ የኾነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም፤ ከ200 ሺህ በላይ ጎብኝዎችንና ከቱሪስቶቹ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ማጣቱን አስታውቋል። ሙዚየሙ ከመጋቢት 8 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ተዘግቷል

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በወይዘሮ ኬርያ ምትክ አዲስ አፈ ጉባዔ ተመረጠ

Adem Farah

ምክትል አፈ ጉባዔውም በአዲስ ተተክተዋል

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 10, 2020)፦ ሕጋዊ በኾነና ሥርዓትን በጠበቀ መንገድ ኃላፊነታቸውን ባለመልቀቃቸው ትችት እየቀረበባቸው ባሉት የቀድሞዋ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ኬርያ ኢብራሒም ምትክ አዲስ አፈ ጉባዔ ተመረጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ምርጫና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ

PM Abiy Ahmed

ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳን አመስግነዋል

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 10, 2020)፦ ሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2012 ዓ.ም. በተካሔደው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በምክር ቤቱ አባላት ከተነሱላቸው ጥያቄዎች መካከል ስድስተኛውን አገር አቀፍ እና ክልላዊ ምርጫን የተመለከተው ይገኝበታል። የምርጫው መራዘምን ተከትሎ በተለይ አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከመስከረም 30 ቀን 2013 ዓ.ም. በኋላ መንግሥት አይኖርም፤ ብጥብጥ ይነሳል በማለት ጭምር እየገለጸ ነው። እንደ ትግራይ ያሉ ክልሎች ደግሞ ምርጫ ካልተካሔደ በክልል ደረጃ ምርጫ እናደርጋለን በማለት እየገለጹ ስላሉት ጉዳይም የቀረበ ጥያቄ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በድጋሚ ቃል አቀባይ ኾነው ተሾሙ

Ambassador Dina Mufti

አምባሳደሩ በአሜሪካ፣ ካናዳ፣ ዙምባብዌ፣ ስዊድን፣ ኬንያና ግብጽ አገልግለዋል

ኢዛ (ማክሰኞ ሰኔ ፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 9, 2020)፦ ከሁለት ዓመት በፊት የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በመኾን ሲያገለግሉ የነበሩትና በኬንያ እና በግብጽ የኢትዮጵያ አምባሳደር በመኾን ሲሠሩ የቆዩት አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፤ እንደገና ቃል አቀባይ ኾነው ተሾሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ በአንድ ቀን 190 የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ተገኙ

Total coronavirus cases in Ethiopia, June 9, 2020

የሟቾች ቁጥር ወደ 32 ከፍ ብሏል

ኢዛ (ማክሰኞ ሰኔ ፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 9, 2020)፦ በኢትዮጵያ በ24 ሰዓታት ውስጥ 190 የሚኾኑ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሪፖርት ተደረገ።

ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 2 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ በተደረገው የጤና ሚኒስቴር ዕለታዊ ሪፖርት 4,599 የላቦራቶሪ ምርመራ ከተደረገላቸው ሰዎች 190ዎቹ በቫይረሱ መያዛቸው ታውቋል። ይህም ባለፉት ሦስት ወራት በአንድ ቀን ከፍተኛ ቁጥር የተገኘበት ዕለት አድርጎታል።

ከ190ዎቹ ውስጥ 153 የሚኾኑት የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በመኾናቸው በአዲስ አበባ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር ከዕለት ዕለት እየጨመረ መምጣቱን የሚያሳይ ኾኗል። በዛሬው ዕለት ቀሪዎቹ ተጠቂዎች 16 ከኦሮሚያ፣ አሥር ከአማራ፣ ሦስት ከሐረሪ፣ ሦስት ከሶማሌ፣ ሦስት ከደቡብና ሁለት ከትግራይ ክልሎች መኾናቸው ታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ባለፉት 24 ሰዓታት አምስት ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተው በመሞታቸው አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 32 ደርሷል። እስካሁን በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥርም 2,336 መድረሱን ሪፖርቱ አመልክቷል።

በአንድ ቀን ውስጥ 18 ሰዎች ያገገሙ በመኾኑም፤ አጠቃላይ ያገገሙ ሰዎችን ቁጥር ወደ 379 ከፍ አድርጎታል። በኢትዮጵያ እስካሁን ምርመራ የተደረገላቸው ሰዎች ቁጥር ደግሞ 152,334 ነው። (ኢዛ)

የ2012 ዓ.ም. 39ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 39th, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ ሠላሳ ዘጠነኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከግንቦት 24 - 30 ቀን 2012 ዓ.ም.) ያሳለፍነውን ሳምንት በጨረፍታ የምናስቃኝበት በዛሬው የሳምንቱ ቅኝታችን አንኳር አንኳር ዜናዎች ውስጥ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በኦነግ ሸኔ የሚፈጸሙ ጥቃቶች በሕወሓት የሚታገዙ ስለመኾኑ መገለጹ አንዱ ነው። ከወታደራዊ እገዛ ጋር በተያያዘ በይፋ የሕወሓት እጅ አለበት በሚል የገለጸበት ሰሞናዊ አነጋጋሪ ወሬ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ