በሕወሓትና በትግራይ ክልል ዙሪያ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ምላሽ
ክልሎች በሙሉ የማዳበሪያ እዳቸውን ሲከፍሉ፤ ያልከፈለው የትግራይ ክልል ብቻ ነው
ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 8, 2020)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ሰኞ ሰኔ 1 ቀን 2012 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርበው ከፓርላማ አባላት ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ ሲባል፤ ከትግራይ ክልልና ከሕወሓት ወቅታዊ አቋም አንፃር አንድ ነገር ይነሳል ተብሎ ይጠበቅ ነበር። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላትም ካቀረቡዋቸው ጥያቄዎች መካከል ይኸው ጉዳይ ተነስቷል። በሌላ አመለካከትም በክልሉ ላይ ጫና ያደርጋል ከሚል መንደርደሪያ ተነስቶ፤ የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችም ተከታትለው የቀረቡበት ነበር።
ሙሉውን አስነብበኝ ...



