የግብጽ የሳይበር ጥቃት ወንጀለኞች በኢትዮጵያ የሳይበር ጥቃት ሙከራ አደረጉ

NISS and Cyber_Horus Group

ጥቃቱ መክሸፉን ኢትዮጵያ አሳውቃለች
ዓላማው ከግድቡ የውኃ ሙሌት ጋር የተያያዘ ነው

ኢዛ (ማክሰኞ ሰኔ ፲፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 23, 2020)፦ መቀመጫቸውን ግብጽ ያደረጉ የሳይበር ወንጀለኞች በኢትዮጵያ የኢኮኖሚና የፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር የተቃጡ የሳይበር ጥቃቶችን ማክሸፉን የኢትዮጵያ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ (ኢመደኤ) አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኮሮና ወረርሽኝ ተጠቂዎች ቁጥር ጭማሪ አስጊ ኾኗል

Total coronavirus cases in Ethiopia, June 20, 2020

በአንድ ቀን 399 ሰዎች ቫይረሱ ተገኘባቸው

ኢዛ (ቅዳሜ ሰኔ ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 20, 2020)፦ በአስጊ ሁኔታ እየሰፋ የመጣው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ በየዕለቱ በቫይረሱ የሚጠቁ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ በመሔድ፤ በአንድ ቀን ብቻ 399 ሰዎች መገኘታቸውን የሚያመለክት ሪፖርት ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 13 ቀን ይፋ ኾኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ ዴክሳሜታዞን የተባለው መድሃኒት ጥቅም ላይ እንዲውል ተወሰነ

Dexamethasone, Total coronavirus cases in Ethiopia, June 19, 2020

የተጠቂዎች ቁጥር አራት ሺህን ተሻገረ
ያገገሙ ሰዎች ከአንድ ሺህ በላይ ኾኗል
የሟቾች ቁጥር በሰባት ጨምሮ 72 ደርሷል

ኢዛ (ዓርብ ሰኔ ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 19, 2020)፦ ለኮሮና ቫይረስ ጽኑ ሕሙማን ያግዛል የተባለውን ዴክሳሜታዞን የተባለውን መድሃኒት እንደ ድንገተኛ ሕክምና ለመጠቀም የኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር መወሰኑ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኮሮናን ለመከላከል የወጣው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማስተካከያ ተደረገለት

Dr. Liya Tadesse, Ministry of Health

የለይቶ ማቆያ ቀናት በግማሽ ቀነሰ፤ የቀብር ሥርዓት እንዲፈጸም ተፈቀደ

ኢዛ (ዓርብ ሰኔ ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 19, 2020)፦ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል በመንግሥት በወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ውስጥ በአስገዳጅነት እንዲተገበሩ ከተደነገጉ መመሪያዎች አንዳንዶቹ እንዲሻሻሉ ተወሰነ። አስገዳጁ የለይቶ ማቆያ ጊዜ በግማሽ ቀነሰ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ2012 ዓ.ም. 40ኛ ሳምንት አንኳር ወሬዎች

Ethiopia Zare's weekly news digest, week 40th, 2012 Ethiopian calendar

የዓመቱ አርባኛ ሳምንት አንኳር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ክንውኖች

ኢዛ (ከሰኔ 1 - 7 ቀን 2012 ዓ.ም.) ያሳለፍነው ሳምንት በኢትዮጵያ ታሪክ በተለዩ ሊታወሱ የሚችሉ የተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች የተወሰኑበት ነው ማለት ይቻላል። ይህም ለመጀመሪያ ጊዜ ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም ላይ ውሳኔ መተላለፉ አንዱ ጉዳይ ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ብዙ ሲያከራክር የነበረው ስድስተኛው አገራዊ ምርጫ እንዲራዘም የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔ ያሳለፈውም ሳምንት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ግብጽ አዲሱ ድርድር ላይ እንቅፋት እየኾነች ነው

ገዱ አንዳርጋቸው

አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የግብጽን አቋም ስስታም ብለውታል

ኢዛ (ረቡዕ ሰኔ ፲ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 17, 2020)፦ በኢትዮጵያ፣ በግብጽና በሱዳን መካከል ለተከታታይ ቀናት ሲካሔድ የቆየው ድርድር አሁንም በግብጽ ግትር አቋም በድጋሚ የተጀመረው ድርድር ላይ እንቅፋት ስለመኾኑ የኢትዮጵያ መንግሥት ይፋ አድርጓል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ ከአውሮፓ ሕብረት 19 ቢሊዮን ብር ድጋፍ አገኘች

European Union

ድጋፉ ከጤናና ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ የሚፈጠር ኢኮኖሚያዊ ቀውስን ለመከላከል የሚውል ነው

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 15, 2020)፦ የአውሮፓ ሕብረት እና አባል አገራቱ የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ለማጠናከር፣ ለለይቶ ማቆያና የማኅበራዊ ጥበቃ ሥርዓቱን ለማጠናከር እና ለተያያዥ ክንውኖች የሚረዳ የ487 ሚሊዮን ዩሮ (19 ቢሊዮን ብር) ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የወላይታ ዞን ተወካዮች በደቡብ ክልል ምክር ቤት ስብሰባ አንሳተፍም አሉ

የወላይታ ዞን

ምክንያታቸው የወላይታ የክልል ጥያቄ ነው

ኢዛ (ሰኞ ሰኔ ፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 15, 2020)፦ በደቡብ ክልል ውስጥ የክልል ጥያቄ ካቀረቡት ዞኖች መካከል አንዱ የኾነው የወላይታ ዞን ተወካዮች፤ በደቡብ ክልል ምክር ቤት ለመቆየትም ኾነ በስብሰባ ለመሳተፍ የማይሹ መኾኑን አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች በ179 ጨምሮ 3,345 ደረሰ

Total coronavirus cases in Ethiopia, June 14, 2020

የሟቾች ቁጥር ወደ 57 ከፍ ብሏል
ጠቅላላ ያገገሙ 545 እንደደረሰም ተገልጿል

ኢዛ (እሁድ ሰኔ ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 14, 2020)፦ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር በየዕለቱ ከፍ እያለ የመጣ ሲሆን፤ ዛሬ እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ በተደረገውም የጤና ሚኒስቴር ሪፖርት መሠረት 179 አዳዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎች በመገኘታቸው አጠቃላይ የቫይረሱ ተጠቂዎችን ቁጥር ወደ 3,345 አሳድጎታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቀድሞ የኢሕአዴግ ንብረትን ለማጣራት ኦዲተሮች ተሾሙ

TPLF, Prosperity Party and NEBE

ሕወሓትና ብልጽግና አንድ የጋራ አጣሪ መምረጥ አልቻሉም

ኢዛ (ቅዳሜ ሰኔ ፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 13, 2020)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቀድሞው የኢሕአዴግ ንብረት ክፍፍልን የቀረበለትን ጥያቄ ለመመለስ የግንባሩን ንብረት የሚያጣሩ ሁለት ኦዲተሮችን መሾሙን አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ