በኮሮና ቫይረስ የሟቾች ቁጥር 14 ደረሰ

Total coronavirus cases in Ethiopia, June 2, 2020

የተጠቂዎች ቁጥር ወደ 1,344 ከፍ ብሏል

ኢዛ (ማክሰኞ ግንቦት ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 2, 2020)፦ በኢትዮጵያ በኮሮና ወረርሽኝ የሞቱ ሰዎች ቁጥር አሥራ አራት መድረሱንና ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ ምርመራ 87 አዳዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎች መገኘታቸውን የጤና ሚኒስትር አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጓ በአምነስቲ መግለጫ ላይ ተናገሩ

Amnesty International

ዓለም እውነቱን እንዲያውቅ እናደርጋለን ብለዋል

ኢዛ (ማክሰኞ ግንቦት ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 2, 2020)፦ ሰሞኑን በአምነስቲ ኢንተርናሽናል የወጣውን መግለጫ ተከትሎ የተለያዩ ተቃውሞዎች እየቀረቡ ሲሆን፣ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤም በዚህ ጉዳይ ላይ የመንግሥት አቋም የሚያንጸባርቅ መልእክት አስተላልፈዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አሳዛኙ ሞት ኮሮና አለብኝ ብላ ራስዋን ያጠፋችው ኢትዮጵያዊ ነፃ ኾነች

Arba Minch University

ወርቅነሽ ዲባባ የ25 ዓመት ወጣት ነበረች

ኢዛ (ማክሰኞ ግንቦት ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. June 2, 2020)፦ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ አሳዛኝ የሚባሉ አጋጣሚዎች እየተስተናገዱ ነው። በኢትዮጵያ የቫይረሱ መከሰት ከተሰማበት ጊዜ ወዲህ አስገራሚ፣ አስጨናቂና ያልተጠበቁ ተግባራት ሲፈጸሙም ታይተዋል። በአርባ ምንጭ በቫይረሱ የተጠረጠረች የ25 ዓመት ወጣት ራስዋን ያጠፋች ሲሆን፤ በተደረገው ምርመራ ከቫይረሱ ነፃ መኾኗ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ በአንድ ቀን የተያዙ ሰዎች ወደ 137 አሻቀበ

Ministry of health and Ethiopian public health institute

በኮሮና የሞተ ሰው ስምንት ደረሰ
109ኙ ከአዲስ አበባ ናቸው

ኢዛ (ዓርብ ግንቦት ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 29, 2020)፦ ከዕለት ዕለት እየጨመረ የመጣው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር አሳሳቢ እየኾነ በመጣበት በዚህ ወቅት በ24 ሰዓት ውስጥ በተደረገ ምርመራ 137 ሰዎች መያዛቸውና የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያና በሱዳን ድንበር ጦርነት ተከፍቶ እንደነበር ተገለጸ

Sudanese soldiers

“አንድ የሱዳን የጦር መኮንን ሲሞት በርካቶች ቆስለዋል” የሱዳን የጦር ቃል አቀባይ

ኢዛ (ዓርብ ግንቦት ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 29, 2020)፦ በኢትዮጵያና በሱዳን ድንበር ላይ በሁለቱ አገሮች ወታደሮች መካከል ጦርነት መከፈቱንና በተካሔደው ውጊያም ሕይወት መጠፋቱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የግንቦት ሃያ የደበዘዘ ትውስታና ምልከታ

አቶ ሙስጠፌ መሐመድ ዑመር፣ ፕሮፌሰር ዶ/ር ሲሳይ መንግሥቴ፣ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና እና አቶ ሚሊዮን አብርሃ

“ግንቦት 20 ለሶማሌ ሕዝብ ካስገኘለት ጥቅም ይልቅ፤ ጉዳቱ ያመዝናል” አቶ ሙስጠፌ መሐመድ፣ የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር

ኢዛ (ሐሙስ ግንቦት ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 28, 2020)፦ ግንቦት 20 ቀን ለማሰብ ትናንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና የትግራይ ክልላዊ መንግሥት (ሕወሓት) ከሰጡት መግለጫ ባሻገር፤ የተለያዩ ክልሎችና ታዋቂ ሰዎች የተሰጡ መግለጫዎች የተለያዩ ምልክታዎች የታዩባቸው ሲሆን፤ ከቀድሞ የውዳሴ ጋጋታ ወጣ ያሉም ኾነው ተገኝተዋል። የኢትዮጵያ ዛሬ ድረገጽ ዝግጅት ክፍልም እነዚሁን የተለያዩ ምልከታዎች ለመዳሰስ ሞክሯል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያና የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ግስጋሴ

Total coronavirus cases in Ethiopia, May 28, 2020

በአንድ ቀን 100 በቫይረሱ የተጠቁ ተገኙ፤ 94ቱ ከአዲስ አበባ የተገኙ ናቸው

ኢዛ (ሐሙስ ግንቦት ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 28, 2020)፦ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ሥርጭት በኢትዮጵያ ውስጥ እጅግ አስጊ ወደሚባል ደረጃ እየተሸጋገረ ስለመኾኑ አመላካች ሪፖርቶች እየወጡ ሲሆን፣ በዛሬው የጤና ሚኒስቴር ዕለታዊ መረጃ በአንድ ቀን 100 የሚኾኑ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች መገኘታቸውን አሳውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ጤና ኮሌጅ በማዕረግ ተመራቂዋ ወጣት ላይ የተፈጸመው አሰቃቂ ግድያ

Addis Ababa Police Commission

የተለያየ የሰውነት ክፍሏን በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት ተወግታ ነው የተገደለችው

ኢዛ (ረቡዕ ግንቦት ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 27, 2020)፦ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የጤና ኮሌጅ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪ ወጣት በቤተ ሙከራ ውስጥ በስለት ተወግታ ሕይወቷ እንዳለፈ ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአስቸኳይ አዋጁ ላይ ማስተካከያ ተደረገ

ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ

የአገር አቋራጭ ትራንስፖርት ታሪፍ 100 በመቶ ዋጋ እንዲጨምር ተወሰነ
የኮድ ሁለት ተሽከርካሪዎች ገደብ ተነስቷል

ኢዛ (ረቡዕ ግንቦት ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 27, 2020)፦ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን መሠረት በማድረግ ተግባራዊ እንዲኾኑ ተወስነው ከነበሩት መመሪያዎች ውስጥ ኮድ ሁለት ተሽከርካሪዎች ላይ ተጥሎ የነበረው የእንቅስቃሴ ገደብን የተመለከተውና በሦስት ሌሎች ጉዳዮች ላይ ማሻሻያ መደረጉ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ