አንድነትም እንደ መአህድ - ብርቱካንም እንደ አሥራት (ሠለሞን አየለ)

የአንባብያን ድምፅ: 4 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Inactive

ሠለሞን አየለ 

በዚህ ጽሑፍ የገለፅኩትን ጉዳይ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሁኔታ የሚከታተሉ ወገኖች ጋር ለመጋራት ከአንድ ወር በላይ ከራሴ ጋር ሙግት ገጥሜአለሁ። አንድነት ፓርቲንም ቀረብ ብዬ ለማጥናት ሞክሬያለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሽምግልናው ነገር (ተመስገን ዘነበ )

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ተመስገን ዘነበ

በተናገረበት ተጽፎ በተናገረበት ወይንም በቴሌቭዥንም ሆነ በመድረክ በታየበት ወቅት ነገሬ ተብሎ ትኩረት ያልተሰጠው ድርጊት አንድ ቀን ዐብይ ጉዳይ ሆኖ ብቅ ይልና የመነጋገሪያ አጀንዳ ይሆናል። የቅንጅት አመራሮች “በሀገር ባህልና ወግ መሠረት” በይቅርታ በተፈቱበት ዕለትም ሆነ በሐምሌ 13 ቀን 1999 ዓ.ም. ሰሞን የተሰጡ መግለጫዎችን፣ የተደረጉ ቃለ ምልልሶችን፣ የተነገሩ የተነበቡ ጉዳዩችን ትኩረት ሰጥቶ ከታሳሪዎች መፈታት በላይም አጉልቶ ያጤናቸው አልነበረም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቫንኩቨር ቅድስት ማርያም ቤ/ክ ውዝግብ በፍርድ ቤት መሰማቱን ቀጥሏል (ዘገዬ በቀለ)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

በላይ፣ ሰብለና፣ ኤርሚያስ ከተከሳሽ ወገን ምስክርነታቸውን ሰጡ፤ ታሪኩም ጀምሯል

ዘገዬ በቀለ - ከቫንኩቨር

ሲጀምር፤ ሲንደረደር

“ቄሱ ሥራቸውን ባግባቡ አልተወጡም፣ በጎሣና በዘር ይከፋፍሉን ነበር። ስብከቱን ትተው ፖለቲካ ያስተምሩን ነበር” ደግሞ ደጋግሞ ይሄንን ነው ያለው ሦስተኛው የዕለቱ ምስክር። ያም ብቻ አይደለም። “እኔ ፍጹም ሥልጣን አለኝ፣ የቤተክርስቲያኗም መሪ እኔ ነኝ፣ ያለኔም ፈቃድ ስብሰባም ውይይትም ሊደረግ አይገባም አሉን። ...” ዝርዝሩ ብዙ ነው። አቶ በላይ ከበደ ገለቱ ይባላል። መልከ መልካምና ረጅም ቁመናው ያማረ፣ ሆን ብሎ ያሳስታል ተብሎ የማይገመት የቤተሰብ ሰው፣ የልጆች አባት፣ በሙያው አካውንታንት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሠለጠነ ማኅበረሰብ ከሚጠይቀው የበዛም ያነሰም አንጠይቅም (ፕ/ር አለማየሁ)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

ፕሬዝዳንት ኦባማ በቅርቡ ለቱርክ ሕግ አውጭዎች አንድ ታሪካዊ ንግግር አድርገውላቸዋል፤ ነገር ግን ይህ ንግግራቸው ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያለውና እስከ አሁን ይፋ ስላልተደረገው የውጭ ጉዳይ ፖሊሲያቸው ጠቃሚ ፍንጭ የሰጠ ነው። ኦባማ ለዓለም ሠላም እየወሰዱ ያሉት እርምጃዎች ለአሜሪካ የውጭ ፖሊሲ በጣም አስፈላጊውን ጤንነት ብቻም ሳይሆን የሚመልሰው አሜሪካ ከተቀረው ዓለም ጋር ለሚኖራት መጪ ግንኙነቶች ድጋፍ የሚሰጥ አዲስ ምሰሶ የሚያቆም ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ስህተቶችን ለማረም የተፈፀሙ ስህተቶች (ርዕዮት ዓለሙ)

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

ርዕዮት ዓለሙ

ማንኛውም ግለሰብ፣ ተቋም፣ ድርጅት ወይም መንግሥት በተለይ ከደረሱበት ችግሮች በመነሳት እንደስህተት የሚያስቀምጣቸው ድርጊቶችና አመለካከቶች ይኖሩታል። ግለሰቡ ወይም ድርጅቱ ስህተቶቹን በትክክል መፈተሽ ካልቻለ በእውነተኛ ስህተቶቹ ፋንታ ስህተት ያልሆኑትን እንደ ስህተት ሊወስዳቸው ይችላል። ይህም እውነተኛውን ስህተት በማረም ፋንታ ሌሎች ስህተቶች የሆኑ “የስህተት ማረሚያ እርምጃዎችን” እንዲወስድ በማድረግ ለተደጋጋሚ ስህተት ይዳርገዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”ሕገመንግሥታዊነት፣ ዲሞክራሲና የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ እስር” ስየ አብርሃ

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

የወ/ት ብርቱካንን እስር ምክንያት በማድረግ ዕሁድ መጋቢት 20 ቀን 2001 ዓ.ም. (ማርች 29 ቀን 2009) በአዲስ አበባ ኢምፔሪያል ሆቴል ”ቃሌ” በሚል ስያሜ በተካሄደው ሲምፖዚየምና የሻማ ማብራት ዝግጅት ላይ አቶ ስየ አብርሃ ”ሕገመንግሥታዊነት፣ ዲሞክራሲና የወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ እስር” በሚል ርዕስ ጽሑፍ አቅርበዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...