እጃችን ለወገኖቻችን የተዘረጋ ይሁን! (ግርማ ካሣ)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ግርማ ካሣ ከቺካጎ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.) ሰኔ 13 ቀን 2000 ዓ.ም.

 

ከአሥራ አምስት ዓመታት በፊት፣ ስለ ኤድስ ለመነጋገር በተጠራ ስብሰባ ላይ፣ አንዲት የዕድሜ ባለጸጋ የሆኑ የሕክምና ባለሞያ የተናገሩት አንድ አባባል ነበር። ያኔ ቀሳፊው የኤድስ በሽታ በሚሊዮን የሚቆጠሩትን ገድሎ፣ የሰው ልጆች ቀንደኛ ጠላት ከተባሉት ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ መከከል የተመደበበት ጊዜ ነበር። ይህ በሽታ ከየት እንደመጣና እንዴት ሊስፋፋ እንደቻለ ሃሳብ የሚሰጡ በርካቶች ነበሩ። ታዲያ እኝህ ሴት የትኩረት አቅጣጫው ወዴት ሊሆን እንደሚገባ ለማስረዳት የአንድ ነብርን ምሳሌ አቀረቡ።

በሻሸመኔ አካባቢ፣ “ድንበር የለሽ ሐኪሞች” የተሰኘው ድርጅት በሚያንቀሳቅሰው የእርዳት መስጪያ ማእከል፣አንዲት እናት ልጇን ስታጥብ

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ደብዳቤ - ለአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ

Star InactiveStar InactiveStar InactiveStar InactiveStar Inactive

እንኩዋን ደስ ያላችሁ! አዲስ ምዕራፍ፣ አዲስ ፈተና

ኢህአዴግ የቅንጅትንና የኢትዮጵያን ትግል ቆዳውን ሊልጠው ትንሽ አቆሰለው እንደሁ እንጂ፡ ውስጡንና ጉዞውን አልቀላውም አይቀላውምም። እነሆ በአዲስ ወኔ፡ በአዲስ ሞራል፡ በአዲስ ስም፡ ነገር ግን በቆየው ኢትዮጵያን ወደ ዴሞክራሲያዊ ስርአት የመመለስ ተልእኮ ጠቅላላ ጉባኤያችሁን ልታደርጉ መሆኑን ሰማን። የኢትዮጵያ እጣ ፈንታ የኢትዮጵያም ድህነት የተቀበረው እዚያው ኢትዮጵያ ውስጥ ነውና በውጭ አገር ህይወት ሳትማረኩ ተመልሳችሁ ከህዝቡ መካከል ለመታገል ወስናችሁ የምታደርጉትን ውጣ ውረድ ሁሉ እናደንቃለን። “ወደፈተናም አታግባኝ” ተብሎ በሚጸለይበት ዓለም እናንተ እያወቃችሁና ሊደርስባችሁ የሚችለውን አደጋ ተረድታችሁ፡ ወደፈተናና ወደፈተና ለመግባት መሰለፋችሁ እለት እለት ያስደምመናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"ሕጋዊ" ዘረፋ፤ የሽፍቶች ካፒታሊዝም በኢትዮጵያ (ዶ/ር ብርሃኑ)

የአንባብያን ድምፅ: 3 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar InactiveStar Inactive

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ " 'ሕጋዊ' ዘረፋ፤ የሽፍቶች ካፒታሊዝም በኢትዮጵያ" በሚል ርዕስ የግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ሣምንታዊ ልሳን በሆነው "የግንቦት 7 ልሳን" በተሰኘው የኢንተርኔት ጋዜጣ የግንቦት 21 ቀን 2000 ዓ.ም. (May 29, 2008) ቁጥር ሦስት ዕትም ላይ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ጉዳይ ላይ ያስነበቡት ጽሑፍ ነው። (በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ!)

ዜና እና ኢትዮጵያ (ባየነው)

የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar ActiveStar Active

ባየነው ከፊንላንድ

በዚህ በኢንተርኔት ዘመን ለሚኖረው ኢትዮጵያዊ በሚቀጥለው ቀን ምን ዓይነት ዜና እንደሚቀርብለት መገመት አይቸግረውም። በቅርቡ በAmerican Chronicle ላይ “Why Europe can not tolerate the existance of 'Ethiopia' “ በሚል ርዕስ በዶ/ር ሙሐመድ ሜጋሎማቲስ የተፃፈው ፅሁፍ '.. the gangster state 'Ethioipia' must be decomposed and broken down to ten pieces, and all the oppressed nations that have been held captive therein must be liberated.' ብሎ ይደመድማል። በርግጥ ከሌሎቹ ፅሁፎቹ እንደተራዳሁት ሰውዬው ፀረ-ኢትዮጵያ (እንደሱ አባባል ኢትዮጵያ የሚለውን ስም እኛ ሰርቀነው ነው) ብቻ ሳይሆን ዘረኝነትንና ጥላቻን፣ ፀረ-ሠላምን የሚያስፋፋ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

የአንባብያን ድምፅ: 3 / 5

Star ActiveStar ActiveStar ActiveStar InactiveStar Inactive

መስፍን ወልደማርያም (ፕ/ር)- ግንቦት 2000

ስማቸው እንደሚያመለክተው፣ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከመንግሥት መዋቅር ውጭ ሆነው፣ ከመንግሥት ምንም ያህል እርዳታ ሳይፈልጉ፣ ራሳቸው ከየትም በሚሰበስቡት ገንዘብ በአገር ውስጥ የሚሠሩ ድርጅቶች ናቸው። የሚሠሩት ምንድን ነው? የሥራቸው ዓይነት በጣም የተለያየና ሰፊ ቢሆንም፣ በሁለት መመደብ የሚቻል ይመስለኛል። አንደኛው በሰብዓዊ ርኀራኄ ላይ የተመሠረተና የሰውን ልጆች መራራ ኑሮ በተቻለ መጠን ለመቀነስና ወደተሻለ መንገድ ለመምራት ነው። ሁለተኛ የተፈጥሮ አደጋ ወይም ሰው-ሠራሽ ቀውስ በደረሰ ጊዜ አስፈላጊውን እርዳታ ለተጎዱት ሰዎች ለማቅረብ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...