የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እናት አቤቱታ

ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን
አዲስ አበባ
ጉዳዩ፡- የልጄ የተመስገን ደሳለኝን ጤንነትና የጉብኝት ሁኔታን ስለማወቅ
የልጄ ተመስገን ደሳለኝን ጉዳይ ይዤ እናንተው ጋር መመላለስ የግድ ሆኖብኝ ዛሬም ከደጃችሁ መጥቻለሁ። ባሕሌና አስተዳደጌ ያስተማረኝ፤ አንድ ቦታ ለአንድ ጉዳይ መመላለስ ለችግሩ ባለቤትም ሆነ ለመፍትሔ ሰጭው አሰልቺ መሆኑን ነው። እውነት ለመናገር ዛሬም ወደ በራፋችሁ ስመጣ እንደው እነዚህን ሰዎች ሥራ እያስፈታኋቸው ይሆን ከሚል ሃፍረት ጋር ነው። ግን ምን ላድርግ? ጉዳዩ ልጅን የሚያኽል የስጋ ክፋይ ነገር ሆነብኝ። እንድትረዱልኝ የምፈልገው እኔም ተቸግሬ እያስቸገርኳችሁ መሆኑን ነው። በተጨማሪም ጭንቀት እረፍት ስላሳጣኝና ጤናዬንም እየፈተነኝ በመሆኑ የመፍትሔ ያለህ እያልኩ አለሁ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...








