ሲያልቅ አያምር፤ “የሥርዓቱን አሟሟት ያሳምርልን!”

Ethiopian PM Hailemariam Desalegn

ያሬድ ኃይለማርያም (ከብራስልስ)

የዛሬ ሦስት ዓመት ታህሳስ 10 ቀን 2007 ዓ›ም “ግፍና አፈና ዐመጽን ይወልዳሉ፤ የዐመጸኛ አፍ ጥልቅ ጉድጓድ ነው (መ.ምሳሌ ም.22፣ ቁ.14)” በሚል አርዕስት ለንባብ ባበቃሁትና በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ በገመገምኩበት ጽሁፍ ይህን ከትቤ ነበር፤ “አንድ ሕዝብ በላዩ ላይ ገዢዎች እየተፈራረቁበት ረዘም ላለ ጊዜ በአገዛዝ ሥርዓት ሥር ስር ሊቆይ ይችል። ይሁንና ዕድሜ ልክ የገዛ አፋኛ ሥርዓት ግን የለም። ሥርዓቱም እንደ ድርጅት፣ ሹማምንቱም እንደ ሰው የጉብዝና ዕድሜያቸው የተወሰነ ነው። የአፈናን ስልት በመለዋወጥና ሸምቀቆውን በማጥበቅም ዕድሜን ማራዘም የሚቻል ቢመስልም በተቃራኒዉ ውድቀትንም ያፋጥናል። ግፉ እየበረታና የመብት ጥሰቱም መረን እየለቀቀ በሄደ ቁጥር የሕዝብ ትእግስት ይሟጠጣል። ሕዝብ መቆጣት ከጀመረና ቁጣውም ወደ አደባባይ አመጽ በተቀየረ ጊዜ የግፍ አገዛዝ ወደ መቃብር፣ ግፈኞቹም ወደ ዘብጥያ እንደሚወርዱ እርቀን ሳንሄድ ባለፉት አምስትና አሥርት ዓመታት ውስጥ በአለም የታዩ ሕዝባዊ ነውጦችንና ያስከተሉትን መዘዝ ማጤን በቂ ነው።” የዚህ ጽሁፍ አላማም የነበረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ደግ ቀን ይመጣል እያለ አምቆ የያዘው ብሶትና ክፌት ሊፈነዳ ጥቂት ስለቀረው ሥርዓቱ በጊዜ እራሱን ያርቅ፤ ካልሆነ ግን የማይቀረው አመጽ ይነሳል። የሥርዓቱም ፍጻሜ እንዳያምር ይሆናል። የሚል ማሳሰቢያ ጭምር ነበር። ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ነገሮች እያፈጠጡ መጡ። ይህን ጽሁፍ ምሉውን ለማንበብ ከዚህ ገጽ ሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ።[1]

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የተቃዋሚ ጎራው ”የወያኔ መውደቂያ ደረሰ” የሚለው ወቅታዊ አጀንዳ መሰረቱ ምን ይሆን?

The End of TPLF

ሸንቁጥ አየለ

”ይሄን ያህል ጄነራል፣ ይሄን ያህል ልብስ አልባሽ፣ ይሄን ያህል ሹም ከዳ፤ እናም ወያኔ ሊወድቅ ነው” እያለ ወቅታዊ አጀንዳውን ያራግበዋል። ጥያቄው ከማን ወገን ነው የከዳው። ሃያ ስድስት ዓመታት ሙሉ ከወያኔ/ሕወሓት ፓርቲ ወይም ጄነራሎች ውስጥ አንድም ኀይል ከድቶ አያውቅም። የወያኔ የሥልጣን ነብስ፣ ልብ፣ አዕምሮ እና ስሜቱ ደግሞ ሕወሓት እና ሕወሓት ብቻ ነው። ለበርካታ ዓመታት እንቶኔ ከዳ፣ እንቶኔ ለቀቀ ሲባል የሕወሓት ጄነራሎች ውስኪያቸውን እያንጫለጡ ይስቃሉ። የሕወሓት ፖለቲከኞችም የተቃዋሚው ሚድያ የሚያርገበግባቸው ሚስጥር የሚመስሉ ነገሮችን አውቀ ይለቃሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"ኢትዮጵያ ኬኛ፣ ጣና ኬኛ!" ድንቅ መንፈስ! (የማለዳ ወግ)

ነቢዩ ሲራክ

* "ጣና ኬኛ!" መልዕክቱ ከእንቦጭ አረሙ በላይ ነው
* የመለያየትና የመፈራረስን አደጋ ያከሸፈ መንፈስ

ከኦሮሚያ "ጣና ኬኛ!" እያለ የተመመው ወጣት ክፉውን የእንቦጭን ዐረም ነቃቅሎ እንደማያስወግድ ግልጽ ነው። ጥቂት ወጣቶች ተሸክመውት ጎጃም የገቡት ዋናው መልዕክት የኢትዮጵያዊነት፣ የአብሮነትና የ"አንድ ነን" እንጂ፤ የእንቦጭ ተራ ዐረም አልነበረም። ኢትዮጵያን የመታደግ የታመቀ ታላቅ መንፈስ ያለው መልዕክት ነበር። ዛሬ ያየሁት ፍቅር፣ ዛሬ ያየሁት የአብሮነት፣ የሕብረትና የአንድነት መንፈስ ከሰፊው የጣና እንቦጭ ዐረም በላይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አባዱላ ገመዳ የእኛ አጀንዳ

ይገረም አለሙ

Abadula Gemeda
አባዱላ ገመዳ

አምና በዚህን ሰዓት፣ ልክ አንደ ሰሞኑ ፓርላማው ሲከፈት ፕሬዝዳንት ሙላቱ አንብቡ ተብሎ የሚሰጣቸውን ይዘው፣ ከፓርላማ ተገኝተው የምርጫ ሕጉን እስከ መሻሻል ሄደን ከተቀዋሚዎች ጋር አብረን እንሰራለን አሉ። ተቃውሞአችው እንደ ዥዋዥዌ ጨዋታ የሆነው አንዳንዶች በዚህ ንግግር ተመስጠው እውነት አደርገውም ወስደው ወያኔ ከመቅጽበት የተፈጥሮ ባህሪውን ይለወጥ ይመሰል አምነውት ሊያሳምኑን ባይሳካላቸውም ትንሽ መንገድ ተንገዳገዱ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አማርኛ ከክርስቶስ ልደት በፊት

ዮፍታሔ

Amharic Language
አማርኛ ቋንቋና ፊደል

የኢትዮጵያ ጥንታዊ ታሪክ ገና ምኑም አልተነካም። አብዛኛው ተቃጥሏል፣ ወድሟል። ከዚህ የተረፈው ተዘርፏል።

በውጭ ሰዎች የተዘረፈው በየቦታው አለ። ነገር ግን ተተርጉሞና ለምርምር አመቺ በሆነ መንገድ ጸሐፍትና ተመራማሪዎች እንዲደርሱበት ሆኖ ለአገልግሎት አልቀረበም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሽሽት እና የአባዱላ ገመዳ ነገር

ክንፉ አሰፋ

Abadula Gemeda
አባዱላ ገመዳ

ከሰሜን እና ከበስተ-ምስራቅ አቅጣጫ እየነፈሰ ያለው አውሎንፋስ መርከብዋን እያናጋት ይገኛል። ጫፍ ላይ ጉብ ያሉትን አስተናጋጆች እያንጠባጠበ የሚገፋው ኀይል እየበረታ መጥቶ፣ አሁን ከካፒቴኑ ቁጥጥር ውጭ የሆነ ይመስላል። ይህ ሁላችንንም የሚያስማማን መራራ ሐቅ ነው። ችግሩ እዚህ ላይ አይደለም። ግን ... እየሰመጠ ካለው ከዚህ መርከብ ለማምለጥ የተገኘችውን ቀዳዳ እየተጠቀሙ የሚሾልኩትን ሁሉ "ጀግና" ብለን ለመጥራት እንደምን ይዳዳን?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“አይትቅትሎ አይትህድኖ” - መምርሂ ሻዕቢያ

ግርማ በላይ

Ethiopia and Eritrea
ኤርትዮጵያ

ግዕዝ/ትግርኛ ለማይረዱ አንባቢዎች ርዕሴን ግልጽ ላድርግ። ርዕሴ በቁሙ ወደ አማርኛ ሲተረጎም፤ “‹አትግደለው አታድነው› - የሻዕቢያ መመሪያ” የሚል ፍቺ ይሰጣል።

ሰሞኑን ከአንድ ትግራዋይና ከአንድ በቀድሞ አጠራር የኤርትራ ክፍለ አገር ተወላጅ ጋር የሞቀ ጭውውት ይዘን ነበር። የልብ ጓደኝነት ያህል በጣም ስለምንግባባ የሆድ የሆዳችንን ነበር የምንጫወተው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ሶሺዮ ፖለቲካ ጉዞ፣ ተግዳሮቶቹና የመፍትሄ ሃሳብ

ገለታው ዘለቀ

የኢትዮጵያ ሶሺዮ ፖለቲካ ጉዞ
የኢትዮጵያ ሶሺዮ ፖለቲካ ጉዞ፤ ወዴት እንሂድ!?

ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ለመገንባት ምቹ የሆነ የሶሺዩ ፖለቲካ ሥርዓት ወደ መፍጠር

(ለአራተኛው የቪዥን ኢትዮጵያ ኮንፈረንስ የቀረበ ጽሁፍ)

የሰው ልጅ ማኅበራዊና ግላዊ ተፈጥሮ ስላለው ለማኅበራዊ ኑሮውና ለግላዊ ኑሮው የተለያዩ ጠገጎችን እያበጀ ይኖራል። እነዚህ የሚሰራቸው ጠገጎች ለግል ሕይወቱም ሆነ ለማኅበራዊ ሕይወቱ ወሳኝ ናቸው። ሰው የዚህን ዓለም ኑሮውን ለመግፋት ከሚያስችሉት መሳሪያዎች አንዱ እነዚህ ጠገጎቹ ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

H.Res 128 በአሜሪካ እንደራሴ ከጸደቀ በሽብር ጉዳይ ላይ ከአሜሪካ ጋር አልተባበርም ማለት ምን አንድምታ አለው?

ገለታው ዘለቀ

Dream of ISIS
የአይሲስ (IS) ሕልም

የተከበሩና የዘወትር የኢትዮጵያ ሕዝብ ነገር የሚቆጫቸው እንደራሴ ስሚዝ ክሪስ የኢትዮጵያን የዴሞክራሲ ትግል ለመደገፍ ሲሉ H.Res 128 ሕግን አርቅቀዋል። ይህ ሕግ በውጭ ጉዳይ በንዑስ ኮሚቴው በሙሉ ድምጽ ጸድቆ ወደ ዋናው ምክር ቤት ለድምጽ ውሳኔ በመሄድ ላይ ነው። ባለፈው ኦክቶበር ሁለት ለሕዝብ ተወካዮች ለድምጽ ይቀርባል ተብሎ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን ይሁን እንጂ እንደተራዘመ ተገልጻል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ክህደትና ድጋፍ መንሳት - የፖለቲከኞች መሰሪ ስልት

ይገረም አለሙ

ተዋከበና

ወዲህ ዘወር ቢል ሰው የለምና

ገብርዬ ሲሞት ቀኙ ዛለና

አረሩን ስቦ ጠጣው ያ ጀግና

ብላቴናው ቴዎድሮስ ካሳሁን አያሌ ዓመታትን ወደ ኋላ በምናብ ተጉዞ ስለ ንጉሥ ቴዎድሮስ የዘፈነው ዘፈን መቅደላ በዓይነ ህሊናችን እንድናይ የማድረግ አቅም አለው። በምስል የምናውቀው ሽጉጥ የጎረሰው ቴዎድሮስ ፈጥኖ ከህሊና ድቅን ይላል። እንዲህ በትውስታ የቴዎድሮስን ምስል እያየሁ በስሜት አንድነት አጥተን በወያኔ በባርነት የመገዛታችን ቁጭት እያንገበገበኝ ከግጥሞቹ መካከል ወዲህ ዘወር ሲል ሰው የለምና የምትለዋ ደግሞ ከመቅጽበት 16 ዓመታት ወደ ኋላ አንደርድራ 2001 ዓ.ም. ላይ ትወስደኝና ሌላ ትውስታ፣ ሌላ ቁጭት፣ ሌላ ወይ ነዶ ውስጥ እያስገባችኝ ተቸግሬአለሁ። ዝግባ የሚያሳቅፍን አንድ ፍቅር አጥተን ሲልማ፣ ምን ብዬ ልግለጸው። ዘፈኑን ማዳማጥ ማቆም ሳይኖርብኝ አይቀርም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ