አዜብ ያለ መለስ፤ የውጭ ሀገር ኑሮና የኢትዮጵያ ተስፋ

አትክልት አሰፋ (ከቫንኩቨር ካናዳ)

አዜብ ያለ መለስ

አሁን…! አሁን…! ባለፈው ሰሞን ነው። ወ/ሮ አዜብ መስፍን መኪና እያሽከረከሩ የትራፊክ ፖሊስ ያስቆማቸዋል። ስህተት ሰርተሻል በማለት ያስቆማቸው ትራፊክ ጥፋቷን ይገልጽላታል። ወ/ሮዋ ጥፋታቸውን አልሸመጠጡም። አዎ አጥፍቻለሁ አንዱን ግን ስታስቆመኝ ተደናግጨ ነው ስህተት የሰራሁት ይላሉ። የትራፊክ ፖለሱም የቅጣት ትኬቱን ጽፎ በጃቸው አስረክቦ የመንጃ ፈቃዳቸውን ይወስዳል። ይሄ በኢትዮጵያ የትራፊክ አሰራር የተለመደ ነው። እናም መንጃ ፈቃድ የሚወሰደው የትራፊክ መምሪያ ተኪዶ፤ ቅጣት ተከፍሎ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሞገደኛው መለስና፤ የሰላማዊ ትግል ተስፋና እውነታ (ክፍል - 2 የመጨረሻ)

ሉሉ ከበደ

የግንቦት 2007 ምርጫ ወያኔ በከፍተኛ አደጋ ላይ ያለ መሆኑን አመልክቷል። የኢትዮጵያን ህዝብ ለውጥ ፈላጊነት በከፍተኛ ደረጃ ያመለከት፤ ህዝቡ ለወያኔ ገዢ ቡድን ለጠባብ ዘረኝነት ርዕዮት ዓለም የጠለቀ ጥላቻ እንዳለው የገለጸ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ መለስ ዜናዊ እንደገመተው ያልተከፋፈለ መሆኑን ያረጋገጠ፤ ከጦርነት ይልቅ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ዘመኑ የሚፈቅደው የፖለቲካ አካሄድ መሆኑን ህዝቡ ጠንቅቆ የተረዳ መሆኑን ወያኔ ራሱ የተረዳበት፤ የወያኔ ባዶነት የተገለጸበትና ሞራሉ እስከመጨረሻው የወደቀበት የታሪክ ምእራፍ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጭለማ ቤት ጓደኞቼ

ሲሳይ አጌና

ልክ የዛሬ አምስት ዓመት በጥቅምት 1999 ዓ.ም. ዓለም በቃኝ ጭለማ ቤት የነበሩት የጭለማ ቤት ጓደኞቼ ዛሬ ተመልሰው ጨለማ ቤት ከወደቁ አንድ ወር አስቆጠሩ፤ ለመብት እና ለነጻነት መቆም፣ ለእውነት እና ለፍትህ መሰለፍ፣ እኩልነት እና ዲሞክራሲ መጠየቅ በወንጀል ተመንዝሮ፣ በአሸባሪነት ተፈርጆ ወህኒ ወርደዋል። ክሱ የፈጠራ፣ ሁሉ ነገር የጨበጣ እንደሆነ ከመነሻው ግልጽ የሆነው የህወሓት መሪዎች ውሸታሞች መሆናቸው ስለሚታወቅ ብቻ አልነበረም፤ ...

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሽቅርቅር ቫንኩቨር፤ የውጭ ሀገር ኑሮና የኢትዮጵያ ተስፋ

አትክልት አሰፋ (ከቫንኩቨር ካናዳ)

ዛሬ ጠዋት በጣም ጠዋት 4 ሰእት ከ11

ገበሬው በጉን ለመሸጥ በግ ተራ ገብቷል። በግተራው ገዥና ሻጭ በርከት ብለው ይተራመሳሉ። በጉን ለመሸጥ ከቆመው ገበሬ ጋር የተጠጋው ገዥ ‘ስንት ናት’ ብሎ አንዷን በግ ይጎትትና ወገቧንም ይፈትሻል። በጓ ታስላለች። እንዴ ምንድነው? ይላል ገዥ ገበሬውን እያየ በመደናገጥ። ገበሬው ዝም ይላል። ከእንደገና ወገቧን ያዝ ያደርጋታል፤ ገዥ። አሁንም በጓ ታስላለች ‘ምን ሆና ነው ታስላለችሳ’ ይላል ገዥ። አሁንም ገበሬ ዝም ይላል። “አትናገርም እንዴ ያስላታል፤ አሟታል እንዴ?” ቢለው ገዥው:   “መሆኑ ነዋ” አለ ገበሬው ጋቢውን ተከናንቦና ውሸት ላለመዋሸት ተጨናንቆ። የሚያስላትን በግ ቢችል ሊሸጥ ነበር ሀሳቡ አስተዳደጉ ውሸትን ስላላስተማረው ውሸቱን መቀላመድና አታሎ መሸጥ አልወደደም። እናም በጓን ለገበያ ቀርባለች፤ ግን ግን በጓ በገበያ ላይ አለችም የለችምም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአዜብ ቀሚስ

W/z Azeb Mesfin ወ/ሮ አዜብ መስፍንዘኢትዮጵያ

ቦታው ኒዮርክ ውስጥ ነው። አፓርትመንት ቪላ የሚሉት አይነት ልዩና ትልቅ የእንግዳ ማረፊያ ነው። ከማረፊያ ሳሎን ውስጥ ጠ/ሚ/ር አቶ መለስ ዜናዊ እና በኒዮርክ የተባበሩት መንግሥታት የኢትዮጵያ ቋሚ  አምባሳደር የነበሩት አቶ ፍስሃ ይመር ብቻቸውን ተቀምጠዋል። አቶ ፍሰሃ ለአቶ መለስ ብርቱ ማብራሪያና ሪፖርት እያቀረቡ (ብሪፍ) እያደረጉ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከዕለቱ ምርጥ አሣዛኝ ዜናዎች ጥቂቶቹ (ነፃነት ዘገዬ)

ነፃነት ዘገዬ

ዓለም በአሣዛኝ ዜናዎች መጥለቅለቅ ከጀመረች ዋል አደር ብላለች። አሁን አሁን የዜና ማሠራጫዎች ራሳቸው ክፉ ዜና ማወጅን በጣም ከመልመዳቸው የተነሣ መልካም ዜናን እንደቅንጦት እያዩት ይመስላል ብዙም ሲማረኩበት አይታዩም። እርግጥ ነው ከወደ አሜሪካን ሀገር በሣተላይት የሚሠራጭ ሱፕሪም ማስተር የሚባል ቴሌቪዥን አውቃለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የካምፓላ ማስታወሻ

Kinfu Assefa ክንፉ አሰፋክንፉ አሰፋ

በምስራቅ አፍሪካ የስራ ጉብኝታችን፤ ከኪጋሊ-ሩዋንዳ ተነስተን አመሻሹ ላይ ካምፓላ ስንገባ ጸሃይ ብርሃንዋን ለጨረቃ አስተላልፋ እልም ብላ ጠፍታለች። ውቧ ካምፓላ በምሽት ከምድር በላይ 2000 ጫማ ርቀት ላይ ስትታይ በከፊል ጨለማና፤ በከፊል ብርሃን ተሸፍናለች። ይህም ከምእራቡ ዓለም ለሚገባ ተጓዥ እንግድነቱ እንዳለ ሆኖ ለጊዜው ግርታን ይፈጥራል። ‘በኢትዮጵያ የምንሰማው የመብራት በፈረቃ አባዜ እዚህም አለ እንዴ?’ ስል ጠየቅሁ ራሴን። ብዙም ሳልውል ግን ችግሩ የተፈጠረው የኡጋንዳ የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫ ጣቢያው "ክፉኛ በመመታቱ" እንደሆነ ሰማሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኢትዮጵያ ኤምባሲ ቅጥፈት በየመን

እንረዳቸዋለን ወይስ እናርዳቸዋለን?

ግሩም ተክለኃይማኖት

የመን መንግሥት ይውረድ በሚሉ ተቃዋሚዎች ከተናወጠች ጀምሮ የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና የወያኔ መንግሥት ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርጉት ቅጥፈታቸውን ለማስተጋባት ነው። አንዳንዴ በመጠኑ መዋሸትም ጥሩ ነው። ባለፈው ረቡዕ ዕለት በዶቼቬሌ ቃላቸውን የሰጡት የኢትዮጵያ ኤምባሲ ቃል አቀባይ አቶ አምደሚካኤል አሳፈሩኝ። አሳፈሩን። ”ኢትዮጵያዊያኑን እንረዳቸዋለን ... ከአይ.ኦ.ኤም. ጋር በመተባበር ወደ ሀገር መመለስ የሚፈልጉትን እንመልሳለን” ብለዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሞገደኛው መለስና፤ የሰላማዊ ትግል ተስፋና እውነታ (ክፍል - 1)

ሉሉ ከበደ

 

ከአበቃቀላቸው አስከ አስተዳደጋቸው፤ ከቤተሰብ አስተሳሰባቸው እስከ አካባቢ እምነታቸው፤ ከጫካ ልምዳቸውና ከተፈጥሮ እውቀታቸው እስከ መናኛ ትምህርታቸው፤ ከግለሰብ እስከ ቡድን እምነታቸው፤ ከጠባብ የዘረኝነት አስተሳሰብ በቀር፤ ከቶም ከቶ ብሄራዊና ኢትዮጵያዊ መንፈስ ያልተፈጠረባቸው፤ የፈጣሪ ስህተቶች፤ እነሆ ኢትዮጵያ ህዝብ ጀርባ ላይ ተፈናጠው ተሸክመናቸው ስንኖር ሀያ ዓመታት ተቆጠሩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ