የመንፈሣውያን ማኅበራት ሀገራዊ አስተዋፅዖ (ከጊዜው ይታየው)
ከጊዜው ይታየው
"ማኅበረ ቅዱሳን በቤተክህነቱ ያገኘውን ቦታ፣ ያቀፋቸው አባላት ያላቸውን ሁሉን ዐቀፍ ዕውቀት፣ ያሰባሰበውን ብሔራዊ ተዋጽኦ፣ የዘረጋውን ዓለም አቀፋዊ መዋቅር ያህል በምሣሌነት ከላይ እንዳነሣናቸው ማኅበራት የጎላ ሀገራዊ አስተዋጽዖ አይታይበትም። ከኃይማኖት ክርክሮች፣ ከመጻሕፍት እና መዝሙሮች፣ ከጉባዔያት እና ስብሰባዎች ባለፈ ለሀገር ዕድገት እና ለህዝቡ ማኅበራዊ አገልግሎት መስፋፋት ብሎም ኅብረተሰቡን ለዕድገት በማነሣሣት ረገድ ዘገምተኛነት አስተውላለሁ።"
ከላይ ያለው "የመንፈሣውያን ማኅበራት ሀገራዊ አስተዋፅዖ" በሚል ርዕስ ጊዜው ይታየው ከፃፉት አስተያየት የተቀነጨበ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
በ1930ዎቹ የኢጣልያ አገዛዝ ሊያበቃ ሲል፣ ክፉ ረሃብ በአዲስ አበባ ውስጥ እንደነበረ አስታውሳለሁ፤ ምናልባትም በገጠር የከፋና ወደ ችጋር የሚጠጋ ሳይሆን አልቀረም የሚል ግምት አለኝ፤ በአፄ ኃይለሥላሴ አገዛዝ ችጋርን በዓይኔ ያየሁበትና ቀምሼው ምንነቱን ያወቅሁበት ነበር። በዚህም ምክንያት ብዙ ተናግሬአለሁ፣ ብዙም ጽፌአለሁ።
የጀመርነው ሃሳብን በነፃነት መግለጽ መቻል፣ መከባበር፣ እውቀትን ከፍ ከፍ ማድረግ ሊበረታታ ይገባል። አንዳችን የሌላኛችንን ሃሳብ ማክበር ስንችል እኛነታችንን ሳይሆን ሃሳባችንን እያብጠለጠልነውና እያብላላነው መሄድ ስንችል በአስመራ መንገድ ይሁን በቸርችል ጎዳና ብቻ ቤተመንግሥት ከች ማለታችን አይቀርም። ሁላችንም የምንተጋው ነፃነታችንን እንድናገኝ ነው። ባርነትን ለመምረጥ እሰጥ አገባው ባላስፈለገንም ነበር። 


