ግንቦት 7 - ዳግማዊ ኢህአፓ ነውን?

አማኑዔል ዘሰላም ጁላይ 25, 2008

"ዶ/ር ብርሃኑ ጠመንጃ አወጁ ይባላል። እውነት ነው እንዴ?" ብሎ አንድ ወዳጄ ደውሎ ጠየቀኝ። ለመመለስ ትንሽ አንገራገርኩኝ። ዘግየት የማለትና የማቅማማት ነገር ታየብኝ። የምመልሰውን አላወኩም ነበር። መሃል መሃል እያረፍኩኝ ዶ/ር ብርሃኑ ከቅንጅት እንደወጡ፣ በአሁኑ ሰዓት በውጭ ሀገር እንደሚኖሩ፣ ግንቦት ሰባት የሚባል አዲስ ድርጅት እንደመሰረቱና የጠመንጃ ትግል ይሁን ምን ይሁን የማይታወቅ የ"አመጽ ትግል" ብለው የሚጠሩትን ለመጀመር እንደወሰኑ ተናገርኩኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዳግማዊ አብዮት (ግርማ ካሣ)

ግርማ ካሣ - ቺካጎ ( This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ) ጁላይ 24, 2008

“እንደ ወንድማማቾች አብረን በሠላም መኖር መልመድ አለብን። አለበለዚያ ሁላችንም እንጠፋለን።” ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ

በቅርቡ በምስራቁ የሀገራችን ክፍል የተቃጠሉና በሳተላይት የተነሱ በርካታ መንደሮችን ተመልክቻለሁ። የአራት ኪሎ ባለሥልጣናት ”እኛ የለንበትም” ብለው አስተባብለዋል። የኦጋዴን ነፃነት ግንባር በበኩሉ ገዢ ፓርቲውን ይከሳል። ማን ተጠያቂ ሊሆን እንደሚችል አብዛኞቻችን የራሳችን ግምት ይኖረናል ብዬ አስባለሁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በሎስ አንጀለስ ያደረገው ንግግር

እሁድ ሐምሌ 13 ቀን 2000 ዓ.ም. (July 20, 2008) ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ በሎስ አንጀለስ ባደረገው ህዝባዊ ውይይት ላይ ንቅናቄውን በመወከል አቶ መስፍን አማን እና አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተገኝተዋል። በዚሁ ህዝባዊ ውይይት ላይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ "የሕግ የበላይነት የሠላማዊና የሠለጠነ ፖለቲካ መሰረት ነው። መለስ ዜናዊ ሕግ በሆነበት ሀገር ግን ..." በሚል ርዕስ ንግግር አድርገዋል። ሙሉውን ንግግር በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!

መተባበር ባንችል እንኳን መሰዳደብ (መዘላለፍ) ብናቆም (ሀገሬ)

ሀገሬ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

መቼም የኢትዮጵያን ፖለቲካና ፖለቲከኞች እንደኔ ከዳር ሆኖ በጥሞና ለሚከታተል ሰው የሀገራችንን ባህልና ወግ ከላወቀ እነዚህ ሰዎች መሰዳደብ፣ መነቋቆር፣ መዘላለፍ፣ ... ባህላቸው ነው ሳይለን አይቀርም። አለመታደል ሆኖ አብረን መብላት እንጂ አብሮ መሥራት በጣም ያስቸግረናል። አብሮ መብላትም አሁን አሁን አየቀረ ነው መሰል። በጋራ የተጀመሩ ብዙ ነገሮችን ስናስተውል መጨረሻቸው መለያየት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“በፋሲካ የተገዛች ባሪያ፤ ሁልጊዜ ፋሲካ ይመስላታል”

ሠላማዊ ወይስ ትጥቅ?

ጋቹዬ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

“የሰዎቹን ሃሳብ አልወደውም፤ የሚሉት ነገር ሁሉ ለእኔ ሕልውና አደገኛ ነው። አትናገሩ የሚላቸው አካል ሲነሳ ግን አሰላለፌ ከሰዎቹ ጋር ነው” ነው ያለው ቮልቴር?

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ሠላማዊ ትግልን ያልፈቀዱ አመጽን ይጋብዛሉ” ጆን ኤፍ ኬኔዲ

ጽናት ፍቅሩ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

የታላቋ አሜሪካ መሪ የነበሩት ጆን ኤፍ ኬኔዲ “those who make peaceful revolution impossible will make violent revolution inevitable” ብለው ነበር። በግርድፉ ስተረጉመው “ሠላማዊ ትግልን ያልፈቀዱ የአመጽ ትግልን ይጋብዛሉ” የሚል ስሜት ይሰጣል። አባባላቸው እውነት ነው። የአመጽን መንገድ መከተል በጣም ቀላል ነው። እጅግ ከባዱ ሠላማዊ ትግልን መከተሉ ነው። በተለይ እንደ አፍሪካ ባለ አህጉር ሠላማዊ ትግል ብዙ መስዋዕትነትን ያስከፍላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በመንግሥትና በኢመማ መሃከል ለነበረው ችግር ምክንያቱና 15 ዓመት የዘለቀው የፍ/ቤት እንግልት በፍትህ አልባ ውሳኔ ስለማክተሙ!!!

Ato Gemoraw Kassaገሞራው ካሣ

በቅድሚያ አንድ ማሳሰቢያ አለኝ። የእኔ ዕቅድና ዓላማ በዚህ ጽሁፍ ለማስተላለፍ የፈለኩትን መልክት መምህራን፤ ተቆርቋሪ ዜጎችና የሚመለከታቸው ወገኖች ሁሉ በቅጡ እንዲረዱልኝ ማድረግ ነው። ስለሆነም የትኛውንም ወገን በማይቆረቁር ቋንቋ መጠቀም ብችል ደስ ባለኝ ነበር። ሆኖም ከስር ከሳሽ ኢመማን ከተከሳሽ ኢመማ መለየት ካልተቻለ ብዥታን ፈጥሮ ለመግባባት ስለሚያዳግት የሚከተለውን አጭር ማሳሰቢያ መስጠት የግድ ብሎኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ሠላማዊ ወይስ ትጥቅ?” - እንካ ስላንቲያዎቹ!

ኩችዬ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

ሰሞኑን በድረ-ገጾች ላይ የማነባቸው አስተያየቶችና ትችቶች ሁለት ቤሳ የምታወጣ ሃሳቤን እንዳካፍል ገፋፉኝ። “ኢህአዴግን ማስወገድ ወይስ መለወጥ?” በሚል ርዕስ ግርማ ካሣ፣ ፕሮፌሰር ማሞ ሙጬ ደግሞ “ሕብረትን በማስቀደም …”፣ ሮቤል አባብያ “አንድነት ፓርቲ ለሚከተለው የሠላም ጎዳና ይሁን ብለናል” በሚሉ ርዕሶች ያስነበቡን ሰነዶች “ሠላማዊ ወይስ ትጥቅ ትግል” በሚለው ትኩስ መነጋገሪያ ነጥብ ዙሪያ የሚያንዣብቡ ናቸው። እነዚህንና ሌሎችንም ጽሑፎች በአቡጊዳ እና በሌሎች ድረ-ገጾች ማንበብ ይቻላል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"ቴዲ አሁንስ የቀረለት አይመስለኝም" ዳኛ ወልደሚካኤል

ዳኛ ወልደሚካኤል መሸሻ

ወያኔ/ኢህአዴግ ለራሱ በአደገኛነቱ አንድ ጊዜ በጥርሱ ከነከሰው፣ በዚህም በዚያም አድረጎ መቦጫጨቁን አይለቅም። ምንን ፈርቶ! ለጊዜው ሁሉም በጁ፣ ሁሉም በደጁ አይደል? መቼም አበው "ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል" ይሉ የለም። እውነታቸውን ነው። ዛሬ ሁሉም አልጋባልጋ የሆነላቸው፣ ያ ቀን እስከሚመጣ ድረስ ነገም ዛሬ ይመስላቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመድረኩ መመስረት መልካም ዜና ነው (ግርማ ካሣ)

የመድረኩ መመስረት መልካም ዜና ነው

ግርማ ካሣ ከቺካጎ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

(በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ)