የግንቦት 7 ንቅናቄ ምንድነው? ምንስ አመጣው? ምንስ ሊያመጣ ይፈልጋል? (አንዳርጋቸው ጽጌ)

"የግንቦት 7 ንቅናቄ ምንድነው? ምንስ አመጣው? ምንስ ሊያመጣ ይፈልጋል?" በሚል ርዕስ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሎንዶን ላይ እሁድ ሰኔ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. (ጁን 22 ቀን 2008 እ.ኤ.አ.) ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ባደረገው ህዝባዊ ስብሰባ ላይ ያደረው ንግግር ነው። ሙሉ ንግግሩን በፒ.ዲ.ኤፍ. ለማንበብ እዚህ ይጫኑ!

 

ግንቦት 7 ንቅናቄ በስዊድን (ያሬድ ክንፈ)

ህዝባዊ ውይይቱ ምን ይመስል ነበር?

ያሬድ ክንፈ ከስዊድን

ሠላምና ጤናውን ከነቤተሰብህ ያበዛልህ ዘንድ የዘወትር ምኞቴ ነው። ለእመቤትህና ለልጃችሁ የከበረ ሠላምታዬን አቅርብልኝ። ዛሬ የማወጋህ “ግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ” የተሰኘውና በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሚመራው አዲስ ንቅናቄ በስዊድን ዋና ከተማ ስቶክሆልም ከተማ ከህዝብ ጋር ያደረገውን ውይይት ነው። ውይይቱ ቅዳሜ ሰኔ 14 ቀን 2000 ዓ.ም. እንደሚካሄድ ስላወቅሁ ከስቶክሆልም 220 ኪሎ ሜትር ርቄ ከምኖርበት ሳንድቪከን ከተማ ወደዚያው አመራሁ። ንቅናቄውን በመወከል ዶ/ር ብርሃኑ እና አቶ ቸኮል ጌታሁን ነበር የተገኙት። አቶ ቸኮል የቀድሞው ቅንጅት የላዕላይ ምክር ቤት አባል የነበረ ሲሆን፣ አሁን በስዊድን ስደተኛ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

«እየሮጡ የሚታጠቁት ፖለቲከኞች» (ፕ/ር መስፍን)

መስፍን ወልደማርያም (ፕ/ር) ሰኔ 2000 ዓ.ም.

በቅርቡ በአንድ ጋዜጣ ላይ ስለ ችጋር በተናገርኹት ላይ አንድ ስሙን የማላስታውሰው ሰው፣ ዛሬ ያለውን የገጠሩን ህዝብ የጥጋብ ኹኔታ ባለማወቄ አዝኖልኝ መልስ ሰጥቶ ነበር። ሰሞኑን በውጭ ቴሌቪዥኖች ከትግራይ እስከ ቦረና የተከሠተውን ችጋር በሚያሣቅቅ ኹኔታ ሲያሳዩን ነበር። ይህን በምጽፍበት ጊዜ ትግራይ ውስጥ ህዝቡ በቤተ ክርስቲያን ተሰብስቦ እግዚኦ እያለ ነው። አለማወቅ የሚባለው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሚባለውን ከሆነ ጸሐፊው ትክክል ነበር። ነገር ግን ችጋርን እና ሞትን መደበቅ በጣም አስቸጋሪ ነውና እያየነው ነው፤ ላስተዋለ ችጋር ያባረራቸውን በአዲስ አበባ መንገዶችም ላይ ያያቸዋል። ይህንን ለማንሣት የተገደድሁት «እየሮጡ የሚታጠቁት ፖለቲከኞችና የትም የማያደርሰው መንገዳቸው» በሚል በአቶ ጌታቸው ረዳ የተጻፈውን ሳነብ በጣም የሚቀራረብ ሀሳብና አስተሳሰብ ስላገኘሁበት ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እጃችን ለወገኖቻችን የተዘረጋ ይሁን! (ግርማ ካሣ)

ግርማ ካሣ ከቺካጎ (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.) ሰኔ 13 ቀን 2000 ዓ.ም.

 

ከአሥራ አምስት ዓመታት በፊት፣ ስለ ኤድስ ለመነጋገር በተጠራ ስብሰባ ላይ፣ አንዲት የዕድሜ ባለጸጋ የሆኑ የሕክምና ባለሞያ የተናገሩት አንድ አባባል ነበር። ያኔ ቀሳፊው የኤድስ በሽታ በሚሊዮን የሚቆጠሩትን ገድሎ፣ የሰው ልጆች ቀንደኛ ጠላት ከተባሉት ውስጥ ከመጀመሪያዎቹ መከከል የተመደበበት ጊዜ ነበር። ይህ በሽታ ከየት እንደመጣና እንዴት ሊስፋፋ እንደቻለ ሃሳብ የሚሰጡ በርካቶች ነበሩ። ታዲያ እኝህ ሴት የትኩረት አቅጣጫው ወዴት ሊሆን እንደሚገባ ለማስረዳት የአንድ ነብርን ምሳሌ አቀረቡ።

በሻሸመኔ አካባቢ፣ “ድንበር የለሽ ሐኪሞች” የተሰኘው ድርጅት በሚያንቀሳቅሰው የእርዳት መስጪያ ማእከል፣አንዲት እናት ልጇን ስታጥብ

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እኛ እና ወላጆቻችን (ያሬድ ክንፈ)

ያሬድ ክንፈ ከስዊድን

ጌታው! ሀገር አማን ናት ወይ? … ስለሀገር ቤቱ ኑሮ ልጠይቅህ አልደፍርም። ምክንያቱም - በቀደም ዕለት እዚህ ስዊድን ከሚኖር ወዳጄ ጋር በስልክ ስንጠርቅ፣ ሀገር ቤት ደውሎ እናቱን “እንዴት ነሽ? … ኑሮስ እንዴት ነው? …” ብሎ ይጠይቃታል፤ እናቱም “… አዬ ልጄ! እጅግ በጣም ጥሩ ነው! በጣም! … በ-ጣ-ም! …” ብላ ትመልስለታለች። ልጅም የእናቱን ጠባይ ስለሚያውቅ “እንዴት?” ብሎ ይላታል። እናትም “ዛሬ ከነገ እንደሚሻል እርግጠኛ ስለሆንኩ” ብላ ሀገር ቤት ያለው ነገር እየባሰ እንጂ እየተሻለ እንደማይሄድ አስረግጣ ስለነገረችው፤ እኔም ከወዳጄ እናት ተምሬ ሀገር ቤት ያለን ሰው ስለኑሮ መጠየቅ እርም ብያለሁ። አንተንም ባለቤትህንም ጭምር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ደብዳቤ - ለአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ

እንኩዋን ደስ ያላችሁ! አዲስ ምዕራፍ፣ አዲስ ፈተና

ኢህአዴግ የቅንጅትንና የኢትዮጵያን ትግል ቆዳውን ሊልጠው ትንሽ አቆሰለው እንደሁ እንጂ፡ ውስጡንና ጉዞውን አልቀላውም አይቀላውምም። እነሆ በአዲስ ወኔ፡ በአዲስ ሞራል፡ በአዲስ ስም፡ ነገር ግን በቆየው ኢትዮጵያን ወደ ዴሞክራሲያዊ ስርአት የመመለስ ተልእኮ ጠቅላላ ጉባኤያችሁን ልታደርጉ መሆኑን ሰማን። የኢትዮጵያ እጣ ፈንታ የኢትዮጵያም ድህነት የተቀበረው እዚያው ኢትዮጵያ ውስጥ ነውና በውጭ አገር ህይወት ሳትማረኩ ተመልሳችሁ ከህዝቡ መካከል ለመታገል ወስናችሁ የምታደርጉትን ውጣ ውረድ ሁሉ እናደንቃለን። “ወደፈተናም አታግባኝ” ተብሎ በሚጸለይበት ዓለም እናንተ እያወቃችሁና ሊደርስባችሁ የሚችለውን አደጋ ተረድታችሁ፡ ወደፈተናና ወደፈተና ለመግባት መሰለፋችሁ እለት እለት ያስደምመናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"ሕጋዊ" ዘረፋ፤ የሽፍቶች ካፒታሊዝም በኢትዮጵያ (ዶ/ር ብርሃኑ)

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ " 'ሕጋዊ' ዘረፋ፤ የሽፍቶች ካፒታሊዝም በኢትዮጵያ" በሚል ርዕስ የግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ሣምንታዊ ልሳን በሆነው "የግንቦት 7 ልሳን" በተሰኘው የኢንተርኔት ጋዜጣ የግንቦት 21 ቀን 2000 ዓ.ም. (May 29, 2008) ቁጥር ሦስት ዕትም ላይ በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ጉዳይ ላይ ያስነበቡት ጽሑፍ ነው። (በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ!)

እኛ በዋርካ (ያሬድ ክንፈ)

ያሬድ ክንፈ ከስዊድን

ሠላምና ጤናህ በምን ሁኔታ ላይ ይገኛል? ባለቤትህና ልጅህሳ? ... እኔ አያልቅበት የተመሰገነ ይሁን አማን ነኝ። ሀገር እንዴት ነች? ... (‘ሀገር’ ስልህ የድሮ ፍቅረኛህን አይደለም፤ ኢትዮጵያን እንጂ) ... በእኔ በኩል ስደትና ስዊድን ሃሪፍ ናቸው፤ ለክፉ አይሰጡም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...