ፕሬዝዳንቱም፣ ጠቅላይ ምኒስትሩም፣ ሕገ መንግሥቱን አያውቁትም
ይገረም አለሙ

ፕሬዝዳንት ሙላቱ በዘንድሮው ፓርላማ መክፈቻ ንግግራቸው አንዳንድ ማሻሻያዎች እንደሚደረጉ ገልጸዋል። የመንግሥቱን ሥልጣን በበላይነት የሚቆጣጠሩት ህወሓቶች የገጠማቸውን የሕዝብ ተቃውሞ ለማስተንፈስ ያስችለናል ያሉትን፤ ግን የማይፈጽሙትን የማሻሻያ ርምጃ ጽፈው ሲሰጡዋቸው ከማንበባቸው በፊት ቢያንስ ሁለት ነገሮችን ሊያገናዘቡ በተገባ ነበር። አንደኛው በአምናው የመክፈቻ ንግግራቸው ከተናገሩት ያልተፈጸሙት ይልቃሉና የማተገብሩትን ተናገር እያላችሁ ቃል አባይ ፕሬዝዳንት አታድርጉኝ ማለት፤ ሁለተኛው ደግሞ የተባሉት ማሻሻያዎች ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ የሚነገሩ ሳይሆን በርግጥ ታምኖባቸው ተፈጻሚ እንዲሆኑ ስምምነት ላይ የተደረሰባቸው ከሆነ፤ አንዳንዶቹ ሕገ መንግሥታዊ ማሻሻያ የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ ሕገ መንግሥቱ በሚፈቅደው መንገድ የሕገ መንግሥት ማሻሻያ እናደርጋለን የሚል በንግግራቸው እንዲካተት ማድረግ ይገባቸው ነበር።
ሙሉውን አስነብበኝ ...



ክንፉ አሰፋ

ይገረም አለሙ


