የአማራ ተጋድሎ ከዚህ ወዴት? (ክፍል ፩)

ሙሉቀን ተስፋው

(ሲያትል በነበረው ስብሰባ ሊቀርብ የነበረ ጽሑፍ ነው፤ ፕሮግራሙ ላይ እንዲቀርብ ለ27 ደቂቃ የተቀዳው ሪከርዱ በቴክኒክ ችግር ባለመሥራቱ መቅረብ አልቻለም፤ እኔም አዘጋጆቹም በጣም አዝነናል። ይህን ጽሑፍ በማዘጋጀት በአዲስ አበባ እና የጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች ያሉ የአማራ ምሁራን አግዘውኛል። ምስጋና ይገባቸዋል፤ ብዙ የአማራ ምሁራን ከጀርባ ሆነው የሚያደርጉት አስተዋጽኦ እጅግ ያስደስታል። በነጻነታችን ጊዜ ስማቸውን ከፍ አድርገን ሥራቸውን እንዘክራለን። ለማንኛውም ላቀርበው የነበረውን ጽሑፍ የመጀመሪያ ክፍል እንሆ!)

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያን የሚጠቅማት ”እኛ” እና “እነሱ” ሳይሆን፤ “እኛ” ብቻ ነው

Half a million Ethiopians protest for regime changeኤፍሬም ማዴቦ

እንደኔ አንዴ ሲቆጥቡት አንዴ ሲደብቁት በድንገት ዕድሜያቸው ወደ ሃምሳዎቹ የገባ ሰዎች አንድ የምንጋራው እምነት አለ፤ እሱም የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች አንድ ነገር መጀመር እንጂ መጨረስ አያውቁበትም የሚል እምነት ነው። በፍጹም ሊፈረድብን አይገባም። ከልጅነት ወደ አዋቂነት የደረስነው ጥንስስ ሲጠነሰስ እንጂ እንጄራውን ሳናይ ነው። ፓርቲ ሲፈጠር እንጂ ውጤቱን ሳናይ ነው። የፖለቲካ ሕብረቶች ተፈጥረው ፈረሱ ሲባል ነው እንጂ፤ እንዲህ አደረጉ ሲባል ሰምተንም አይተንም አናውቅም። ባጠቃላይ የፖለቲካ ትግል ሲባል ነው እንጂ፤ ድል ሲባል ሰምተን አናውቅም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት የቀረበ የሥራ ማመልከቻ

አመልካች ነፃነት ዘለቀ

Oromo protesters (Photo: Reuters)

የኢትዮጵያ የሽግግር መንግሥት በቅርብ እንደሚመሠረት እገምታለሁ። አሁን ይህን የሥራ ፈላጊ ማመልከቻ የማስገባው ማንም ሳይቀድመኝ ከአሁኑ የአንድ ዕጩ ቦታ ለመያዝና ተወዳድሬ ካለፍኩ ቀጥዬ የምጠቁመው የሥራ ቦታ ላይ ተመድቤ ለመሥራት ነው። የማመለክትበት የሥራ ቦታ በኢትዮጵያ የታራሚዎች አስተዳደር ዋና የኃላፊነት ቦታ ነው። ለምን እንደመረጥኩት አስረዳለሁ። በቅድሚያ ግን ...

ሙሉውን አስነብበኝ ...

"እውነትን እንጂ ውሸትን አናስተናግድም" [የማለዳ ወግ]

Mesfin Bezu of TG television* የምርጫው ትዝታዬ ... * የጅብ ችኩል ...

ነቢዩ ሲራክ

መቼም ይህ የአሜሪካ ምርጫ ከቅስቀሳው እስከ ትራንፕ ምርጫ ትዝታው ብዙ ነው። በመጨረሻው ቀንና በምርጫው ውጤት ቀን የሆንነው ግን በጣም ያጓጓና ልዩ ትዝታ ይዞ ያለፈ አጋጣሚ ነበር። ለብዙዎቻችን ... የማልረሳውን የእኔን ትዝታ ከትዝብት ጋር ላጋራችሁ ...

"እውነትን እንጂ ውሸትን አናስተናግድም!" የሚል መርኅን ይዘው ከሚንቀሳቀሱት የቲጂ ቲቪ አዘጋጅ ጋዜጠኛ መስፍን በዙ "HILLARY WINS!" "ሂላሪ አሸነፈች!" የሚል አንድ አስገራሚ ሰበር መረጃ ከሌሊት 3:34 a.m. ተሰራጭቶ ደረሰኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከአሜሪካኖቹ ምርጫ አንድ ነገር ብቻ መማር በቂ ነው

ሸንቁጥ አየለ

U.S. President Barack Obama shakes hands with Donald Trump

አሜሪካኖቹ የተዋጣለት ሥርዓት እና ተቋም በመገንባታቸው ብቻ የተለያዩ ውስብስብ እና አስቸጋሪ አስተሳሰቦችን እና ዕይታዎችን ይዘው የሚመጡ ፖለቲከኞችን ማስተናገድ የሚችል ሁኔታን፤ ብሎም አሜሪካ እንደ አገር የምትቀጥልበትን ጥልቅ መሰረት ጥለዋል። ለምርጫ ሲወዳደሩ ያለው ሂደት፣ ምርጫው ሲጠናቀቅ የሚያሳዩት የሠለጠነ ባህሪ እና የሥልጣን ሽግግሩ አስደማሚ ሂደት ሁሉ የአንድ ነገር ውጤት ነው። ተገቢውን ሥርዓት እና ተቋም በመገንባታቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለአዋጁ አዋጅ

ይገረም አለሙ

ኢትዮጵያውያን ለሃያ አምስት ዓመታት ባካሄድነው ትግል ከወያኔ አገዛዝ መላቀቅ አልቻልንም። በዚሁ መንገድና ስልት ቀጥሎም ከወያኔ አገዛዝ መላቀቅ እንደማይቻል ከመቼውም ጊዜ አሁን ግልጽ ሆኗል። ሕዝቡ በራሱ ተነሳሽነትና መንገድ ባካሄደው ትግልና እሱን ተከትሎ ወያኔ የወሰደው የአስቸኳይ ጊዜ ርምጃ በግልጽ ያሳየንም ይህንኑ ነው። ስለሆነም እስካሁን በተከተልነው አሠራርና በተጓዝንበት መንገድ ከወያኔ አገዛዝ ለመገላገል እንደማይቻል በመረጋገጡ ባልተሄደበት መንገድ ለመሄድ ይቻል ዘንድ ከሕዝቡም በኩል የአስቸኳይ ጊዜ ማወጅ አስፈላጊ ይመስለኛል። በዚህ የምትስማሙ ከዚህ በታች በቀረበው መነሻ ሃሳብ ላይ አስተያየት ስጡበት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከ“አማራ ይደራጅ” መፈክር ጀርባ …? ለጥሞና ውይይት

አመለ በየነ

በቅድሚያ ተማጽኖ፣

1. ትግሉ የሕዝብን የሥልጣን ባለቤትነት ለማረጋገጥ ይሁን!

ለራስ ሥልጣን አልሞ የሚደረግ ትግል ለምንይልክ ቤተመንግሥት አይደለም ለፓርላማ ወንበርም እንዳላበቃ አይተናል፣ አልተማርንበትም እንጂ ቤተ መንግሥት ደርሶም መገፍተር እንደሚያስከትል በኦነግ አይተናል፣ እናም ይቅር ተዉት፣

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሥርዓት ለውጥ በሥርዓት

Girma Seifu Maru. Photo TheGuardianግርማ ሰይፉ ማሩ

የሰሞኑን የካቢኔ ሹመት አስመልክቶ ብዙ አስተያየት እየተሰጠ ነው። አስተያየት መስጠቱ ትክክል ነው። በሕይወታችን ላይ ከፋም-ለማም ውሳኔ የሚያሳልፉ ሰዎች ምደባ በመሆኑ የመሰለንን አስተያየት መሰንዘር ተገቢ ይመስለኛል። በእኔ እምነት ኢህአዴግ ባልሆንን ሰዎች፣በተለይ ደግሞ የተሻለ አማራጭ ይታየናል፣ አለንም ለምንል ዜጎች ዋናው ጉዳይ የኢህአዴግ ፖሊሲ በምን ዓይነት ካቢኔ በደንብ ተግባራዊ እንደሚሆን መምከር አይመስለኝም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

”ጥልቅ ቅሌት”

WHO Director General Candidate Dr Tedros Adhanom.ወለላዬ ከስዊድን

ግብዝና አላዋቂ ሰዎች ጊዜና አጋጣሚ ፈቅዶላቸው በሥልጣን ላይ ሲቆዩ የእውቀትና የትልቅነታችው መጠን የት ድረስ እንደሚያደርሳቸው የሚገምቱበት ማስተዋል የላቸውም።

ሁሉንም የተካኑ፣ ለሁሉም ነገር ተመራጮች፣ ብልህና አዋቂዎች አድርገው እራሳቸውን ስለሚገምቱ ስህተት ላይ ይወድቃሉ።

ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኃኖም ለዓለም የጤና ድርጅት ዳይሬክተርነት ለመወዳደር ቀርበው ያሳዩን ይሄንኑ የሚያመላክት ነው። አጠያያቂ ጉዳይ ግን አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“ጃዋር፦ ያልተናገረውን በተናገረው ውስጥ መስማት”

Jawar Mohammedታፈሰ ወርቁ

“ወያኔ አንድ ታንክ ከመግዛት፣ በ10 ሚሊዩን ዶላር አንድ ከፋፋይ አክቲቪስት መግዛት ትመርጣለች” መስፍን ፈይሳ ሮቢ

ጋዜጠኛ ምናላቸው ስማቸው በ“አፈርሳታ” ዝግጅቱ ጃዋርን አቅርቦ አነጋግሮት ነበር። ለጃዋር የቀረበለት አንዱ ጥይቄ “... የግንቦት ሰባት እና የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባርን ጥምረት እንዴት አየኸው?” የሚል ነበር። ጃዋር “... ቅን አመለካከት ነው ያላቸው ... ጥሩ ሙከራ እያደረጉ ነው ... ኢንቴንሽናቸው ቅን ነው ...” ብሎ በተናገረው ውስጥ “... በትክክል የተሠራ ግን አይደለም፣ የፖለቲካ ብስለት ያለበት ግን አይደለም” የሚል እና ያልተናገረውንም ነገር (between the lines) ትሰማለህ። ነገሩ “ከኛ ወዲያ ፉጭት አፍ ሟሞጥሞጥ ነው ...” ወይም “... ፖለቲካ ከኔ ወዲያ ላሳር ነው” የሚል ድምጸት አለው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ