የበጎው ሰው፣ የጎልማሳው ህልፈት (የማለዳ ወግ)

ነቢዩ ሲራክ

"... በሕብረት መኖር አለብን ብሎ የሚመክር የሚዘክር ድንቅ ሰው ነበር፣ አቡኬ"

Abukee Alex, አቡኬ አሌክስ

በያዝነው ሣምንት ... በአብዛኛው የሐበሻ መገናኛ መንደር፣ በማኅበራዊ ድረ ገጽ ዋንኛ መድረክ በFacebook መስኮት አንድ መሪር መርዶ ተሰምቷል። የትሁት፣ አስተዋይና አርቆ አስተዋዩ በጎ ሰው፣ የጎልማሳው የአቡኬ አሌክስ ህልፈት። የአቡኬ አሌክስ በድንገት መለየት ጥልቅ ኀዘናን ሁላችንንም አንገብግቦናል። "ከሞቱ አሟሟቱ" እንዲሉ አቡኬ ባንድ ጀንበር ታይቶ በርቶ፣ ባንዱ ጀንበር ሳይታሰብ ጠፍቶብናል። እናም በቅርብ ከሚያውቁት፣ ቤተሰብ ዘመድ አዝማድ ጓደኞች እኩል በሥራው በዝና የምናውቀው በኀዘኑ አዝነን ከፍቶናል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከአብርሃም ደስታ እስከ ሀብታሙ አያሌው

Habtamu Ayalewነቢዩ ሲራክ

የማለዳ ወግ ... የሀገሬ ዲሞክራሲያዊ የበቀል ፖለቲካ

የሰሜኑ ኮከብ አብርሃ ደስታ እንኳንም ተፈታህ!

የሰሜኑ ኮከብ ወንድም አብርሃም ደስታ ከእስር እንደሚፈታ ቢገመትም ዘንድሮ ሲሆን እንጅ ሲባል ለማመን ተቸግሬያለሁና ዛሬን መቆየት ነበረብኝ ። እናማ የሰሜኑ ኮከብ ደፋሩና ለእውነት ግንባሩን የማያጥፈው የመቀሌው አብርሃም ደስታ "እውነት ተፈታ" ሲባል ሰማሁ፣ ደስ አለኝ! አብርሽ፤ እንኳንም ከቤተሰብ፣ ከዘመድ አዝማድና ወዳጅ አፍቃሪ ወገንህ ጋር ተቀላቀልክ እልሃለሁ፣ አብርሽ!

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ባበደች ሀገር ውስጥ መኖር

ምሕረቱ ዘገዬ

ወዳጅን ቢከፋውም ጠላት ግን ደስ ይበለው - ሀገራችን በአሁኑ ወቅት ለይቶላት ጨርቋን ጥላ ዐብዳለች። ዕብደት እንዴት ይገለጻል? የሀገርና የሕዝብ ዕብደት እንደኔ አስተሳሰብ በሚከተሉት ሁኔታዎች ሊገለጽ ቢችል የሚያስማማ ይመስለኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከዐውሬ ጋር ትግል

ነፃነት ዘለቀ

ትግል ከሰው ጋር እንጂ ከዐውሬ ጋር ከሆነ አደገኛ ነው። ህወሓት ከጥንስሱ ጀምሮ መቼም ቢሆን በሰዎች ተመርቶ አያውቅም። ይህ ድርጅት ከመነሻው በሰው መሰል አራዊት እንደሚመራ የታወቀ ሆኖ ሳለ ከእባብ ዕንቁላል ዕርግብ ይፈለፈል ይመስል ከዚህ ቡድን መልካም ነገርን የሚጠብቁ ሞኛ ሞኝ ፍጡራን ሲስተዋሉ የሚገርም ነው። እነዚህ የህወሓት ሰዎች የራሳቸው ጠባብ የአስተሳሰብ አድማስ ከፈጠረላቸው የትግሬ ዘር ውጪ ሌላውን ሰው በሰውነት ሊቀበሉ አይፈልጉም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከእንግሊዝ ከአውሮፓ ሕብረት መውጣት የምንማረው

አንዱዓለም ተፈራ

Brexit የእንግሊዝ ከአውሮፓ ሕብረት መውጣት

የዓለም የንዋይ ስምሪት አውታር ክንፎች አጥናፋቸውን ሲያሰፉ፣ የዓለም አቀፍ የፖለቲካ ቁልልፍ እየተወሳሰበ ሲሄድ፤ ግለሰቦች ከራሳቸው ከባቢ ውጪ ያለውን ክንውን፤ በንቃት መከታተል ግድ ይሆንባቸዋል። ምክንያቱም በዚህ በተወጠረ የዓለም ትስስር ሕልውና፣ አንዱ አካባቢ የሚነጥረው ጠጠር ሌላውን አካባቢ ያረግባልና! ለዚህ ነው ከኢትዮጵያ በስደት አሜሪካ ተቀምጬ፤ አውሮፓ የሚካሄደውን የእንግሊዝ ከአውሮፓ ኀብረት መውጣት በንቃት የተከታተልኩት። እናም እነሆ ግንዛቤዬ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጳጳሶችና ስደት

ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም

እንዲያውም ርእሱን ካህናትና ስደት ብለው ይሻላል፤ ካህናት የሁሉንም ሃይማኖቶች መሪዎችን ይመለከታል፤ ዓላማዬም ሁሉም የኃይማኖት መሪዎችን የሚነካ ነው፤ ነገር ግን የእኔ እውቀት በክርስትናው ላይ ጎላ ያለ በመሆኑ የክርስቲያኖቹ መሪዎች ላይ ያተኮርኩ ቢመስልም ሁሉንም ይመለከታል፤ በተለይ መነኩሴዎች ላይ የማነጣጥርበትም የተለየ ምክንያት አለኝ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት የምንበቃው፣ በአለት ላይ የቆመ ፓርቲ ሲኖረን ነው

ይገረም አለሙ

አቶ ግርማ ሠይፉ ማሩ / Girma Seifu Maru

ከ2002 ዓ.ም. እስከ እስከ 2007 ዓ.ም. ድረስ የፓርላማ አባል የነበሩት አቶ ግርማ ሰይፉ "ለዴሞክራሲ ሥርዓት ምን ዓይነት ፓርቲ ያስፈልገናል?" በሚል ርዕስ ያቀረቡትን ጽሁፍ ለማንበብ የጓጓሁት የአንድነት ም/ሊቀመንበር ነበሩና ከተግባር ተሞክሮአቸው በመነሳት ድክመት ጥንካሬን መለስ ብለው ቃኝተው መሆን ያለበትን ያመላክታሉ በሚል ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለዴሞክራሲ ሥርዓት ምን ዓይነት ፓርቲ ያስፈልገናል?

ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ (በግራ) ዶ/ር መረራ ጉዲና (በቀኝ) / Prof. Beyene Petros (Left) & Dr. Merera Gudina (Right). (AP Photo/Mulugeta Ayene)ግርማ ሠይፉ ማሩ

በሀገራችን የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበራት እንዲሁም የሚዲያ ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ እንደሆነ ሁሉም ይረዳዋል ማለት ባይቻልም፤ በተለይ የፖለቲካ ፓርቲ አባል አመራር የሆኑ ሰዎች ይጠፋቸዋል ብሎ የሚገምት ላይኖር ይችላል። እውነቱ ግን ከዚህ የተለየ ነው። በአሁኑ ጊዜ የፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ ሰዎች የሚሳተፉት በዋነኝነት በሀገራችን የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ያላቸውን መዋጮ በማስላት ሳይሆን፤ ገዢውን ፓርቲ በማስወገድ ላይ ብቻ ያጠነጠነ ይመስላል። ይህንንም ማድረግ የሚፈልጉት ደግሞ በትርፍ ጊዜያቸው ከሥራ መልስ ወይም በጡረታ ጊዚያቸው ነው። ይህን ሲያደርጉ ደግሞ የብዙ ወጣቶች ጊዜና ጉልበት መስመር ባልያዘ አቅጣጫ እንደሚመሩ አይረዱም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአፍሪካ ቀንድ ተስፋ ሊኖረው ይችላልን?

የአፍሪካ ቀንድ ተስፋ ሊኖረው ይችላልን? Horn of Africaፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም (ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ)

እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2014 “ለአፍሪካ ተስፋ ሊኖረው ይችላልን?“ በሚል ርዕስ አንድ ትችት ጽፌ ነበር። ያንን ትችት የጻፍኩት ባለፉት ጥቂት አስርት ዓመታት ውስጥ ተንሰራፍቶ በሚገኘው እና ማቆሚያ በሌለው በአፍሪካ ሰው ሰራሽ ቀውስ ምክንያት ምንም ዓይነት ተስፋ የሌለኝ በመሆኑ ነበር። እ.ኤ.አ ሚያዝያ 2014 የመካከለኛው አፍሪካ ሬፐብሊክ (መአሬ) አውዳሚ በሆነ የጎሳ-ኃይማኖት የዘር ማጥፋት ዘመቻ እልቂት ውስጥ ተዘፍቃ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቡ የሻዕቢያ እና የህወሓት እንጂ የህዝብ አይደለም

ግርማ ካሳ

ሰሞኑን በሰሜኑ የሀገራችን ግዛት ጦርነት ተቀስቅሷል። አስመራም፣ አዲስ አበባም ያሉ ገዢዎች ጦርነት መደረጉን ማመን ብቻ ሳይሆን “ይሄን ደመሰስን፣ ይሄን ያህል ገደልን” እያሉ በመማጸደቅ ላይ ናቸው። ዓለም የትናየት ደርሳለች፣ ትላንናት እኛ እየረዳናቸው ነጻ የወጡ የአፍሪካ ሀገራት እንኳን የትናየት ደርሰዋል፣ እኛ አሁንም መግደልን እንደ ጀብዱ አድርገን እናወራለን።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ