የመለስ ... ጉዞ - "ሸውራራ ብትኳል ለትዝብት" (አረጋዊ በርሀ)

አረጋዊ በርሀ (ዘሔግ)

በቅርቡ “መለስ ዜናዊ እና የህወሓት የትግል ጉዞ” በሚል ርዕስ፣ ፀሐፊ ኢያሱ መንገሻ (ኮ/ል) ተብሎ፣ ባለ 313 ገፆች አንድ መጽሐፍ መጋቢት 2002 ዓ.ም. አዲስ አበባ ታትሞ ወጥቶ፤ ከጫፍ እስከ ጫፍ አነበብኩላቸው። መጽሐፉ አቶ መለስን ልዩ የታሪክ ካባ ለማልበስ ሲባል ብዙ የተደከመበት የፈጠራ ቅንብር መሆኑ ገና ከሽፋኑና ከመቅድሙ ያስታውቃል። ለዚሁም በተጨማሪ ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ ከባህል ሚኒስትሩ ጋር በመሆን በሸራተን ሆቴል ደግሰው ነሐሴ 22 ቀን 2002 ዓ.ም. መርቀውለታል። ፀሐፊው ኮ/ል ኢያሱ መንገሻ ይባል እንጂ፤ በዚህ የፈጠራ ቅንብር የአቶ መለስ እጅ በእጅጉ እንዳለበት ብዙ ጠቋሚ ነጥቦች በዚህ መጽሐፍ ይገኛሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቆንጂት ብርሃን አስነበበችን (ነሲቡ ስብሐት)

በ”ምርኮኛ” መጽሐፍ ላይ የግል አስተያየት

ነሲቡ ስብሐት (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)

በአንድ ብዕር ሁለት መጽሐፍ። የዚያን ትውልድ ተጋድሎና የዘመኑን መቅሰፍት። በአንድ በኩል በወጣትነት ዘመኑ ያ ትውልድ ለሀገሩ አንድነት፣ ለሰው ልጆች መብትና ለዴሞክራሲ ያደረገውን ተጋድሎና የከፈለውን መስዋዕትነት፤ በሌላ በኩል የዛሬው ወጣቶች ደግሞ በኤች.አይ.ቪ. ቫይረስ የተጠቁትን ወገኖች በግብረ ሰናይ ድርጅቶች አማካይነት የሚያደርጉትን እንክብካቤና ሕይወት አርዝም ጥረት።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቆነጃጅት፣ ወይንና ቅኔ

አበራ ለማ

Alemayehu Taye's booksይድረስ ለሥነኪን ተጠባቢው አለማየሁ ታዬ - ታለህበት

ይህች ሂሣዊ ንባብ አከል ማስታወሻዬ ትድረስህ። እንደ ተጋባዥ የሥነ ግጥም የኔታ ሁኜ፣ አንተ ደግሞ የ”ፍካታ የሥነ-ጽሑፍ ክበብ” ታሊባን* ሁነህ የዛሬ አሥራ ምናምን ዓመታት በፊት እንደተዋወቅን ከላክልኝ መልዕክት ተረድቻለሁ። የዘሩት በቅሎ፣ አሽቶ፣ ፍሬውም ጎምርቶና በስሎ ከማየት በላይ ላንድ ገበሬ ምን የሚያስደስተው ፀጋ አለ? የኔና ያንተም ትውውቅና ቁርኝት በዚህ ሊመሰል ታድሏልና እሰየው ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

'ሕገ-ወጥ ድርጊት ተፈፀመብኝ' የሚል ከሕገ-ወጦች ጋር አያብርም

Syie Abrha's bookታምራት ታረቀኝ

አቶ ስየ አብርሃ መጽሐፍ ጻፉ ሲባል ለማግኘት ጉጉት ያደረብኝ ከደደቢት እስከ ምኒልክ ቤተመንግሥት በነበረው ጉዞ አበይት የሆኑትን ይልቁንም ሌላው ተራ ታጋይ ሊያውቃቸው የማይችላቸውን ግን ትውልድ ሊያውቃቸው ታሪክም ሊመዘግባቸው የሚገቡ ጉዳዮችን ይተርኩልናል በሚል ስሜት ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ያቶ ስየ ስንክሳር ለኔ እንደተሰበቀኝ

ነፃነትና ዳኝነትጌዲዎን በለጡ

የዛሬው ትኩረቴ መጥሐፉ በጥቅል ሃሳቡ ባስተላለፈልኝ ፍሬ ጉዳይ ላይ ብቻ ያነጣጠረ በመሆኑ እንዲያ ብቻ ይተርጎምልኝ፤ ባለ 439 ገጹ “ነፃነትና ዳኝነት” ስለያዘው ዝርዝር ጉዳይ የተገለጠልኝን ያህል ለማለት በሌላ ጊዜ እመለስበታለሁ። ለወጉ ይመቸኝ ዘንዴ አለፍ አለፍ ብዬ በመግቢያቸው በመጀመሪያውና በሁለተኛው አንቀጽ የተጠቀሰውን ላመል መነካካት አሻኝ፤ ...

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የስየ አብርሃ ሚስጥሮች” (ዘውገ ፋንታ)

የተስፋዬ ገብረአብ የመጽሐፍ-ሂሱ ሂስ

Zewge Fanta“Freedom & Justice in Ethiopia” - By Siye Abrahaዘውገ ፋንታ

መግቢያ

ደራሲው ተስፋዬ ገብረአብ፣ ስየ አብርሃ ስለጻፈው “ዝባዝንኬ” መጽሐፍ ባቀረበው “የመጽሐፍ ሂስ” ሌላ ሂስ መጻፍ ለማይቀርብ ምግብ እጅ ማስታጠብ ይሆናል። የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ተስፋዬ ገብረአብ ስለ ስየ መጽሐፍ ማሾፉን ለመቃወም ወይም ስየን ለመደገፍ አይደለም። ስየ ይህን ከጠበቀ በውጤቱ ሊበሳጭ ይችላል። ተስፋዬ ገብረአብም የስየ መጽሐፍ ውሸት የዋጠው ነው ያለውን ይህ ፀሐፊ ቢደግፍም የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ሲገለጽ የሚያረካው አይሆንም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...