”የፍርድ በትር በማናለብኝነት ንፁኀን ላይ የሚለጠፍ መርግ አይደለም”
ከቴዲ አፍሮ ጉዳይ ጊዜያዊ ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ (ዲሴምበር 16 ቀን 2008)
Ethiopia Zare (ኀሙስ ታህሳስ 9 ቀን 2001 ዓ.ም. December 18, 2008)፦ በቅርቡ የተቋቋመመውና መጠሪያ ስሙ ”የቴዲ አፍሮ ጉዳይ ጊዜያዊ ኮሚቴ” የተሰኘው በአርቲስት ታማኝ በየነ የሚመራው ኮሚቴ በቴዲ አፍሮ ጉዳይ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ አወጣ።
”የፍርድ በትር በማናለብኝነት ንፁኀን ላይ የሚለጠፍ መርግ አይደለም”
ከቴዲ አፍሮ ጉዳይ ጊዜያዊ ኮሚቴ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ (ዲሴምበር 16 ቀን 2008)
ስለፍትህ፣ ስለፍቅርና መቻቻል በማቀንቀኑ ምክንያት በሕግ ሽፋን እየተፈፀመበት ያለውን በደል ተከትሎ፤ ”የፐርዥያ የንጋት ወፍ በመባል ከምትታወቀው ከማርዘይህ፣ ከግሪኳ ሙሉና ሜርኩሪና ከብሪታኒያዋ ቫኔሳ ፌዴግሬቭ ተርታ ሊሰለፍ ይገባዋል” የሚል ምስክርነት የተሰጠለት ኢትዮጵያዊው ድንቅ አርቲስት ወጣት ቴዎድሮስ ካሳሁን፤ ባሳለፍነው ሣምንት በተከሰሰበት ጉዳይ የ6 ዓመት እስራትና የ18 ሺህ ብር ቅጣት እንደተጣለበት ለሁላችንም ግልፅ ነው።
(ሙሉውን ጋዜጣዊ መግለጫ በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ)