ለሚመለከታቸው የኢትዮጵያ ጉዳየኞች (Stakeholders) በሙሉ
ከለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የተላለፈ ጥሪ
ሁላችንም እንደተከታተልነው በኢትዮጵያ ተካሄደ በተባለው ”ምርጫ” የመለስ ቡድን የ99.6% አብላጫ ድምጽ በማግኘት ”አሸንፌያለሁ” ማለቱ እንኳንስ ተቃዋሚዎችን የራሱ ደጋፊዎች አፍ ያስያዘና መልስ ያሳጣ ሆኖ ሰንብቷል።ከዚህ አኳያ ባለፈው ነገር ላይ ብቻ እያተኮርን ”ምንድነው ስህተታችን?” እያልን ጊዜ ከማጥፋት ይልቅ ለነጻነታችን እና ለዘመናት በሰቆቃ ለሚኖረው ህዝባችን ምን ልናደርግ እንችላለን የሚለውን በመጠየቅ በቀጣይነት በጋራ ልናደርግ በሚገባን ነገር ላይ ውሳኔ መድረሱ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።ይህንን አብሮ የመሥራትን እና የአንድነትን ነገር ሁሉም በየፊናው እያነሳ የሚወያይበት ዕለታዊ አጀንዳ እንደሆነ ከየአካባቢው ይሰማል። ወቅታዊው ጥያቄም ”ከሁሉ በፊት ነጻነታችን” የሚለው እንደሆነ ይደመጣል። ሙሉውን አስነብበኝ ...