አ.አ. ውስጥ አንበሣ አውቶቡስ 2 ሰዎችን ገድሎ 10 አቆሰለ
Ethiopia Zare (ሰኞ ሚያዝያ 27 ቀን 2000 ዓ.ም. May 5, 2008)፦ትናንት ከሰዓት በኋላ አዲስ አበባ ውስጥ አንበሣ አውቶቡስ ፍሬን ተበጥሶበት ከገጫቸው ሰዎች ውስጥ ሁለቱ ሲሞቱ አስሩ በከባድ ሁኔታ መቁሰላቸውን የኢትዮጵያ ዛሬ ሪፖርተር ከአዲስ አበባ ዘገበ።
አደጋው የደረሰው ፒያሣ ውስጥ የሚገኘው አያሌው ሙዚቃ ቤት አካባቢ አውቶቡስ በመጠበቅ ላይ በነበሩ ሰዎች ላይ ነው።
አደጋው የደረሰባቸው ሰዎች የሕክምና እርዳታ እንዲያገኙ ወደ ሆስፒታል የተወሰዱ መሆናቸው ታውቋል።



