አ.ሰ.አ.ድ.ድ.ማ. የአንድነት ፓርቲን ሕጋዊ ፈቃድ አስመልክቶ መግለጫ አወጣ

Ethiopia Zare (ሰኞ ነኀሴ 19 ቀን 2000 ዓ.ም. August 25, 2008)፦ ”አንድነት ሰሜን አሜሪካ የድጋፍ ድርጅቶች ማኅበር” የተሰኘውና በሰሜን አሜሪካ የሚገኘው የአንድነት ፓርቲን ሕጋዊ ፈቃድ ማግኘት ተንተርሶ ”አንድነት ፓርቲ በአዲስ ምዕራፍ ይጀመራል!” በሚል ርዕስ መግለጫ አወጣ። በዚሁ መግለጫው ላይ ማኅበሩ ለፓርቲው የሚያስፈልገውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚሰጥ ቃል ገብቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሪፖርተር ጋዜጣ ባለቤትና ዋና አዘጋጅ ከአ.አ. ጎንደር ተወስዶ ታሰረ

Amare Aregawi, Publisher & Editor-in-chief of Reporter Ethiopia Zare (ሰኞ ነኀሴ 19 ቀን 2000 ዓ.ም. August 25, 2008)፦ በሀገር ውስጥ በእንግሊዝኛ እና በአማርኛ የሚታተመው የ”ሪፖርተር” ጋዜጣ ባለቤትና ዋና አዘጋጅ አቶ አማረ አረጋዊ ዓርብ ነኀሴ 16 ቀን ከቢሮው ተወስዶ ጎንደር ውስጥ በእስር ላይ እንደሚገኝና ዛሬ ሰኞ ነኀሴ 19 ቀን ጎንደር ውስጥ ፍርድ ቤት እንደሚቀርብ የኢትዮጵያ ዛሬ ምንጮች ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የከፍተኛ ፍርድ ቤት መዝገብ ቤት ኃላፊ በጉቦ ቅሌት ታሠሩ

‘በኢትዮጵያ ጉቦ ህጋዊ ይመስላል’ አስተያየት ሰጭዎች

Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 18 ቀን 2000 ዓ.ም. August 24, 2008)የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ክፍል፣ የመዝገብ ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ታዬ ተኮላ፣ ለልምምድ (አፓረንትሺፕ) ከመጣ ተማሪ ላይ 200 ብር ጉቦ ሲቀበሉ፣ እጅ ከፍንጅ ተይዘው የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሏቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የከፍተኛ ፍርድ ቤት መዝገብ ቤት ኃላፊ በጉቦ ቅሌት ታሠሩ

‘በኢትዮጵያ ጉቦ ህጋዊ ይመስላል’ አስተያየት ሰጭዎች

 

 

Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 18 ቀን 2000 ዓ.ም. August 24, 2008)የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአስተዳደር ክፍል፣ የመዝገብ ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ታዬ ተኮላ፣ ለልምምድ (አፓረንትሺፕ) ከመጣ ተማሪ ላይ 200 ብር ጉቦ ሲቀበሉ፣ እጅ ከፍንጅ ተይዘው የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሏቸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሦስተኛ፣ አራተኛና ሰባተኛ ወጡ

Ethiopia Zare (እሁድ ነኀሴ 18 ቀን 2000 ዓ.ም. August 24, 2008)፦ በቤጂንጉ ኦሎምፒክ ዛሬ በተደረገው የወንዶች ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ሦስተኛ፣ አራተኛ እና ሰባተኛ በመውጣት ውድድሩን አጠናቀዋል። ኢትዮጵያ ሁለተኛዋን ነኀስ ለማግኘት ችላለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቀነኒሳ በቀለ ሁለተኛውን የኦሎምፒክ ክብረወሰን ሰበረ

Kenenisa Bekele, Beijing olympic, 20080823, 5000 men

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ነኀሴ 17 ቀን 2000 ዓ.ም. August 23, 2008)፦ በዛሬው ዕለት በቤጂንግ ኦሎምፒክ በተካሄደው የወንዶች 5 ሺህ ሜትር የፍፃሜ ሩጫ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ለ24 ዓመታት በሞሮኮዋዊው ሰዒድ አዊታ ተይዞ የነበረውን የኦሎምፒክ ክብረወሰን በመስበር ለኢትዮጵያ አራተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል። በ10 ሺውም የኦሎምፒክ ክብረወሰንን መስበሩ አይዘነጋም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ፓርቲ ዛሬ ፈቃድ ተሰጠው

UDJ certificate
 

Ethiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 16 ቀን 2000 ዓ.ም. August 22, 2008)፦ ለወራት የፓርቲ ፈቃድ ለማግኘት ሲጠባበቅ የነበረው አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዛሬ ከምርጫ ቦርድ ፈቃዱን በእጁ ያስገባ መሆኑን የአዲስ አበባ ምንጮቻችን አስታወቁ። (ከላይ የሚመለከቱት ለአንድነት ፓርቲ ከምርጫ ቦርድ የተሰጠው ሕጋዊ የምስክር ወረቀት ነው፤ የምስክር ወረቀቱን አሳድገው ለማየት ከፈለጉ እላዩ ላይ ይጫኑት!) 

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያውያንና ሶማሊያውያን ስደተኞች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ታገዱ

Ethiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 16 ቀን 2000 ዓ.ም. August 22, 2008)፦ የአሜሪካ መንግሥት ቤተሰብን ከቤተሰብ በማገናኘት ፕሮግራሙ፣ ወደ አገሩ የሚገቡ የኢትዮጵያና የሶማሊያ ስደተኞች ላይ እገዳ ጣለ። የስቴት ዲፓርትመንት ዕገዳ የተጣለባቸው በተለይ የምሥራቅ አፍሪካ ሀገሮች፣ በመጠኑ ደግሞ የላይቤሪያ ስደተኞች መሆናቸው ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጥሩነሽ ዲባባ ሁለተኛዋን የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች

Tirunesh Dibaba, after she won 5,000 m. in Beijing Olympic, 20080822

Ethiopia Zare (ዓርብ ነኀሴ 16 ቀን 2000 ዓ.ም. August 22, 2008)፦ ዛሬ በቤጂንግ ኦሎምፒክ በተደረገው የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ርቀት ፍፃሜ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ አንደኛ በመውጣት ለራስዋ ሁለተኛውን፣ ለኢትዮጵያ ደግሞ ሦስተኛውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች። አትሌት መሠረት ደፋር ደግሞ ሦስተኛ በመውጣት ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የነኀስ ሜዳሊያ አስገኝታለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት የጉቦ ቅሌት ድራማ

በጉቦ ቅሌት የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት መዝገብ ቤት ኃላፊ ታሰሩ

Ethiopia Zare (ኀሙስ ነኀሴ 15 ቀን 2000 ዓ.ም. August 21, 2008)፦ የ50 ዕድሜ ባለፀጋ የሆኑትና ለ30 ዓመታት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያገለገሉት፣ የፍ/ቤቱ የአስተዳደር ክፍል የመዝገብ ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ታዬ ተኮላ ከአ.አ.ዩ. ተማሪ ላይ 200 ብር ጉቦ ሲቀበሉ እጅ ከፍንጅ ተያዙ። ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ። የታሪኩ ድራማ እንደሚከተለው ይገኛል ...

ሙሉውን አስነብበኝ ...