በወ/ት ብርቱካን የሚመራው ላዕላይ ምክር ቤት ነገ አርብ ይሰበሰባል
Ethiopia Zare (ሐሙስ የካቲት 20 ቀን 2000 ዓ.ም. February 28,2008)፦ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ በተ/ም/ሊ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራው የላዕላይ ምክር ቤት ነገ አርብ ስብሰባ እንደሚያካሂድ ታማኝ ምንጮች ጠቆሙ።
Ethiopia Zare (ሐሙስ የካቲት 20 ቀን 2000 ዓ.ም. February 28,2008)፦ የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲ በተ/ም/ሊ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራው የላዕላይ ምክር ቤት ነገ አርብ ስብሰባ እንደሚያካሂድ ታማኝ ምንጮች ጠቆሙ።
ፍርዱ አግባብ አይደለም ያሉ መምህራን ታፈሱ
‘ውሳኔው ኢ-ፍትሀዊ ነው’ አቶ ገሞራው ካሣ
Ethiopia Zare (ረቡዕ የካቲት 19 ቀን 2000 ዓ.ም. February 27,2008)፦ በ1941 ዓ.ም. የተቋቋመውና ቀደም ሲል በዶ/ር ታዬ ወልደሰማያት ይመራ የነበረው አንጋፋው የመምህራን ማህበር ከ15 ዓመታት የፍርድ ሙግት በኋላ በ1985 ዓ.ም. ለተመሰረተውና በኢህአዴግ ተቀጥላ ለሆነው ቡድን የተወሰነ መሆኑን ከአዲስ አበባ የደረሰን መረጃ ጠቆመ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...(ሰኞ የካቲት 17 ቀን 2000 ዓ.ም. February 25,2008)፦ በኢትዮጵያ ትልቁንና የመጀመሪያውን የካንሰር ሆስፒታል ለመገንባት የገቢ ማሰባሰቢያ እና ግንዛቤ ማስጨበጫ ኮንሰርት በሚሌኒየም አዳራሽ ይዘጋጃል፡፡
ዘ ላይፍ ሰከንድ ቻንስ ፋውንዴሽን ከሠራዊት መልቲ ሚዲያ ጋር በመተባበር በየካቲት 22 ቀን 2000 ዓ.ም. በሚሌኒየም አዳራሽ የሚደረገው ኮንሰርት ዓላማ፤ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን 80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በኦሮሚያ ክልል ሸኖ ከተማ ላይ ለሚገነባው የካንሰር ሆስፒታል የመጀመሪያውን የገቢ ማሰባሰቢያ እና ግንዛቤ ማስጨበጫ ይዘጋጃል፡፡
ሙሉውን አስነብበኝ ...Ethiopia Zare (እሁድ የካቲት 16 ቀን 2000 ዓ.ም. February 24,2008)፦ በተለያዩ ድረ-ገጾች ላይ ሰሞኑን የተለቀቀው የሲቪል ማኅበረሰብ ረቂቅ አዋጅ አፋኝ ይዘት ያለው ነው ሲሉ አንዳንድ የሕግ ባለሙያዎች አስተያየት ሰጡ።
የሕግ ባለሞያና የሲቪል ማኅበረሰብ አባል እንደገለጹት፤ በሕግ ማርቀቅ ሂደት የሲቪል ማኅበረሰቡና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት እንዲሳተፉ በመንግሥት በኩል ፈቃደኝነት እንዳልነበረ ገልጸው፤ አሁንም ቢሆን ወጣ የተባለውን ረቂቅ አዋጅ ከድረ-ገጽ ላይ ወስዶ ከማየት ውጭ በመንግስት በኩል የተገለጸ ምንም ነገር እንደሌለ ተናግረዋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...Ethiopia Zare (ቅዳሜ የካቲት 15 ቀን 2000 ዓ.ም. February 23,2008)፦ የ"ሰለፊያ" ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ ኢብራሂም መሐመድ እና የ"አልቁዱስ" ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ አቶ ኢዘዲን መሐመድ የካቲት 8 ቀን በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አንድ ዘገባ ጠቆመ።
የአልቁዱስ አሣታሚና የአቶ ኢዘዲን መሐመድ ባለቤት ወ/ሮ ማሪያ ቃዲም ከባለቤታቸው ጋር ታስረዋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ..."ኢ/ር ኃይሉ በሌሉበት መነጋገር አንችልም" የአቶ አባይነህ ቡድን
"ኢ/ር ኃይሉ ሻውል የሚመጡበትን ቁርጥ ቀን ንገሩንና እናራዝመው ..." እነ ወ/ት ብርቱካን
"ኢ/ር ኃይሉ ሻውል በሦስት ምክንያቶች ቶሎ ወደ ኢትዮጵያ አይመለሱም፤ አንደኛው የጤናቸው ሁኔታ ነው፣ ሁለተኛው ደግሞ አሜሪካን ሀገር ባሉት አባላት መካከል ብዙ የተበላሹ ነገሮች ስላሉ እሱን ለማስተካከል ሲሆን ሦስተኛው ከግል ሕይወታቸው ጋር የተያያዘ መሆኑ ..." የኢንጂንየር ኃይሉ ባለቤት
ሪፖርታዥ
Ethiopia Zare (ዓርብ የካቲት 14 ቀን 2000 ዓ.ም. February 22, 2008)፦ ከእስር የተፈቱት የቀድሞው ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ አመራሮችን በጋራ አሰባስቦ እንዲነጋገሩ ለማድረግና ድርጅቱን እንደ ድርጅት ለማስቀጠል ጥረት ሲያደርግ የነበረው 17 አባላት ያሉት የሽማግሌዎች ስብስብ በመጨረሻ ባወጣው መግለጫ ሁለት ለ 15 ልዩነት የፈጠሩ መሆናቸውንና አብዛኞቹ ለሽምግልናው አለመሳካት መንስኤው ኢ/ር ኃይሉ ሻወል መሆናቸውን ከአዲስ አበባ የደረሰን ዘገባ አስረዳ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...Ethiopia Zare (ቅዳሜ የካቲት 8 ቀን 2000 ዓ.ም. February 16,2008)፦ የሰሜን አሜሪካ የቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ድጋፍ ሰጪዎች ማኅበር በሚያደርገው የቦርድ ምርጫ አቶ ክፍሌ ጥግነህ ተገኝተው ሊያስመርጡ መሆኑን አንድ ዘገባ ጠቆመ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...Ethiopia Zare (ዓርብ የካቲት 7 ቀን 2000 ዓ.ም. February 15,2008)፦ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያለውን የአዲስ አበባን ነዋሪን ገቢ ባላገናዘበ መልኩ የአንበሣ አውቶቡስ ከ25 እስከ 50 ሣንቲም የታሪፍ ጭማሪ በማድረጉ የከተማው ነዋሪ በከፍተኛ ሁኔታ መማረሩ ተደመጠ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...Ethiopia Zare (ዓርብ የካቲት 7 ቀን 2000 ዓ.ም. February 15,2008)፦ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የፎቶ ጋዜጠኞች ማኅበር በዚህ ሣምንት መቋቋሙ ታወቀ። የማኅበሩ መጠሪያ ስም "ብሔራዊ የፎቶ ጋዜጠኞች ማኅበር" ሲሆን፣ ፕሬዝዳንቱ አቶ ቢንያም መንገሻ መሆናቸው ታውቋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...አከራዮቹን ደህንነቶች እያስፈራሩ ነው
Ethiopia Zare (ማክሰኞ የካቲት 4 ቀን 2000 ዓ.ም Feb. 12,2008)፦ በምክትል ሊቀመንበሯ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የሚመራው የቅንጅት ሥራ አስፈጻሚ በአንድ የሕግ ባለሙያ አማካኝነት የተከራዩትን ቢሮ የቤቱ ባለቤትና አከራይ የወያኔ ደህንነቶችና የቀበሌ ደንብ አስከባሪዎች ለሕገወጥ ተግባር ቤቱን አከራይተሻል በሚል ጫና በማሳደራቸው ምክንያት በዛሬው ዕለት አስለቅቃቸዋለች።
ሙሉውን አስነብበኝ ...