የመናኸሪያው ፍንዳታ የስምንት ሰው ሕይወት ቀጠፈ
ከምርጫ 97 ወዲህ በተከሰቱ 13 ፍንዳታዎች 36 ሰዎች ሲሞቱ ወደ 200 ሰዎች ቆስለዋል
(ሪፖርታዥ)
Ethiopia Zare (እሁድ ጳጉሜን 2 ቀን 2000 ዓ.ም. September 07, 2008)፦ በአዲስ አበባ በአውቶቡስ ተራ አካባቢ "መናኸሪያ" ሊደርስ ትንሽ ሲቀረው በተከሰተው አሰቃቂ ፍንዳታ የሞቱት ሰዎች ቅጥር ስምንት የደረሰ ሲሆን፣ በሃያ አራት ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የመቁሰል አደጋ ደርሷል። አሰቃቂውን ፍንዳታ በሚመለከት ዝርዝር ዘገባ እንደሚከተለው ተጠናቅሯል።
ለአራት ዓመታት ወደሠራችበት ፎቶ ቤት ስታመራ ከወትሮው የተለየ ችግር ይገጥመኛል ብላ ያላሰበችው የ20 ዓመቷ ወጣት ሃና ጎሣዬ (በፎቶግራፉ ላይ የምትታየው)፣ ከመኖሪያ ቤቷ አቅራቢያ ወደሚገኘውና ለሀገር አቀፍ መናኸሪያ (አውቶቡስ ተራ) የተጠጋውና መርካቶ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሥራ ቦታዋ “ፎቶ ሻርፕ” የሄደችው በእግሯ ነበር።
ሙሉውን አስነብበኝ ...





