የግንቦት ሰባት ንቅናቄ በኑርንበርግ ህዝባዊ ስብሰባ ክፍል ፩

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 7 ቀን 2000 ዓ.ም. June 14, 2008)፦ ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ዛሬ ረፋዱ ላይ በጀርመን ኑርንበርግ ከተማ ከደጋፊዎቹና ከኢትዮጵያውያን የሚያደርገውን ህዝባዊ ውይይት መጀመሩ ታወቀ። በዚህ ህዝባዊ ውይይት የንቅናቄው መሥራቾች የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አቶ መስፍን አማን እንደተገኙ ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፖሊስ በአንድነት ጽ/ቤት ጉባዔው እንዳይካሄድ ከለከለ (7፡40 ሰዓት)

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 7 ቀን 2000 ዓ.ም. June 14, 2008)፦ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ መሥራች ጉባዔውን ለማድረግ ዛሬ ጠዋት በኢምፔሪያል ሆቴል ሊያደርገው ያቀደውን ጉባዔ ፖሊስ ያስተጓጎለው ሲሆን፣ በመቀጠልም በፓርቲው ጽሕፈት ቤት ከሰዓት በኋላ ሊካሄድ የነበረውን ስብሰባ ፖሊስ ጽ/ቤቱን በመክበብ ተሰብሳቢዎቹ ቅጽር ግቢውን ለቅቀው እንዲወጡ ትዕዛዝ እየሰጠ መሆኑን ከስፍራው ለኢትዮጵያ ዛሬ የደረሰው ዘገባ አስረዳ።

በአንድነት ፓርቲ ቢሮ ድንኳን እየተተከለ ነው

"ሥራ አስፈታናችሁ፤ እናንተም ሂዱ እኛም መሄዳችን ነው" ፕ/ር መስፍን

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 7 ቀን 2000 ዓ.ም. June 14, 2008)፦ በኢምፔሪያል ሆቴል አካባቢ ብዛት ያለው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ጉባዔተኞች የተነኙ ሲሆን፣ ብዛት ያላቸው ወጣቶችም የድርጅቱ መስራች በመሆን የተገኙ መሆናቸውን አረጋግጠናል። ወጣቶቹ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የነበሩና በተለያዩ ቦታዎች በኃላፊነት የሚሠሩ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ምንጮቻችን ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢምፔሪያል ሆቴል በፖሊስ ተከቧል

"የምርጫ ቦርድ የፈቃድ ደብዳቤ የላችሁም" ፖሊስ

"ስብሰባውን ለማካሄድ ከደህንነት ፈቃድ ተሰጥቷል" ኢምፔሪያል ሆቴል

Ethiopia Zare (ቅዳሜ ሰኔ 7 ቀን 2000 ዓ.ም. June 14, 2008)፦ ዛሬ ጠዋት ጠቅላላ የፓርቲውን የመሥራች ጉባኤው የጠራው አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ የስብሰባ ቦታው በፖሊስ በመከልከሉ ምክንያት በኢምፔሪያል ሆቴል ይደረግ የነበረው ስብሰባ በድርጅቱ ቢሮ ለማካሄድ መታቀዱ የተገለጸ ሲሆን፣ ዛሬ ጠዋት ኢምፔሪያል ሆቴል በፖሊስ መከበቡን ታማኝ ምንጮቻችን ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አንድነት ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ መሥራች ጉባዔውን ያካሂዳል

የስብሰባ አዳራሽ መከልከል ጉባዔውን እንደማያስቀረው ተገለጸ 

Ethiopia Zare (ዓርብ ሰኔ 6 ቀን 2000 ዓ.ም. June 13, 2008)፦ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ነገ ቅዳሜ ሰኔ 7 ቀን 2000 ዓ.ም. የሚያደርገው የመሥረታ ጠቅላላ ጉባዔ በስብሰባ አዳራሽ መከልከል ምክንያት እንደማይስተጓጎል ኢንጂንየር ግዛቸው ሺፈራው ገለጹ። ጠቅላላ ጉባዔው በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ጽሕፈት ቤት ውስጥ ነገ ከሰዓት በኋላ ይደረጋል ብለዋል።

የምርጫ 97 ጉዳይ በስዊድን ፓርላማ ውይይት ላይ ተነሳ

“በምርጫ 97 በኢህአዴግ መንግሥት ላይ ጠንካራና ተግባራዊ ተፅዕኖ ባለመወሰዱ በሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም ተመሳሳይ ፀረ-ዴሞክራሲያዊ ተግባራት ባልተደገሙ ነበር” በስዊድን የአንድነት ድጋፍ ማኅበር ተወካዮች

Ethiopia Zare (ረቡዕ ሰኔ 4 ቀን 2000 ዓ.ም. June 11, 2008)፦ ስለዚምባብዌ ተቃዋሚዎች የስዊድን ሊበራል ፓርቲ በፓርላማ ባዘጋጀው ውይይት ላይ ተገኝተው የተወያዩ ሲሆን፣ የአንድነት ፓርቲ ደጋፊዎችም ተገኝተው ምርጫ 97ን ተከትሎ ኢህአዴግ ለወሰዳቸው እርምጃዎች በወቅቱ የስዊድን መንግሥትን ጨምሮ ምዕራባውያን ተግባራዊ ተፅዕኖ ወስደው ቢሆን ኑሮ፤ በዚምባብዌና በሌሎችም የአፍሪካ ሀገራት ተመሳሳይ የምርጫ ማጭበርበር ባልተከተለ ነበር ሲሉ ተቹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ በተከሰተው ድርቅ ላይ የተጠናከረ ልዩ ዘገባ

“ሕፃናት ብቻ 6 ሚሊየን ተርበዋል” ቢቢሲ

“ሕፃናቱ 75 ሺህ ብቻ ናቸው” ኢህአዴግ

“20 ሚሊየን ዶላር ያስፈልጋል” ኢህአዴግ

“ኢትዮጵያ ለገጠማት የምግብ እጥረት 197 ሚሊየን ዶላር እርዳታ ያስፈልጋታል” ተመድ

“ድርቁ በሱማሌ፣ ከፊል ኦሮሚያና ደቡብ ላይ ነው የተከሰተው” አቶ አዲሱ ለገሠ

“ድርቁ በምዕራብ አርሲ፣ በሻሸመኔ፣ በደቡብ አዋሳ ዙሪያ፣ በወላይታ ዞንና በምሥራቅ ሐረርጌ ተሰራጭቷል” ዩኒሲኤፍ

“በግብርናው ባሀብቶች እንዲሳተፉበት ካልተደረገ መቼም ቢሆን በምግብ ራሣችንን አንችልም” የተከበሩ አቶ ቡልቻ ደመቅሣ

Ethiopia Zare (ማክሰኞ ሰኔ 3 ቀን 2000 ዓ.ም. June 10, 2008)፦ በኢትዮጵያ የተከሰተውን ድርቅ አስመልክቶ ኢህአዴግ የተጎጂዎችን ቁጥር ዝቅ አድርጎ እየተናገረ ሲሆን፤ በሌላ በኩል ደግሞ የውጭ ሚዲያዎች፣ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች፣ ለጋሽ ድርጅቶች አኀዙ ከፍተኛ መሆኑን እየገለጹ ይገኛሉ። ሁሉም ወገኖች በዚህ የበልግ ዝናብ እጥረትን ተከትሎ ሀገሪቱን እያጠቃ ባለው ድርቅ ላይ የሚሉትን የኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ በጽሑፍና በምስል በማቀናበር እንደሚከተለው አቅርቦታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሎንዶኑ ህዝባዊ ውይይትና ተያያዥ ዜናዎች ዝርዝር ዘገባ

የፊታችን ቅዳሜ ግንቦት 7 ንቅናቄ ለመጀመሪያ ጊዜ በአውሮጳ ከህዝብ ጋር ይወያያል

Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 2 ቀን 2000 ዓ.ም. June 9, 2008)፦ ትናንት በእንግሊዝ ዋና ከተማ ሎንዶን ላይ በእንግሊዝ የቅንጅት ድጋፍ ኮሚቴ አዘጋጅነት የተካሄደው ህዝባዊ ስብሰባ ከተጠበቀው በላይ በርካታ ታዳሚ በመገኘቱ ሠፋ ወዳለ አዳራሽ የተዛውሮ፣ በተሳካ ሁኔታ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ ጥቂት ግለሰቦች ለመቃወም ሙከራ ያደረጉ ቢሆንም እንዳልተሳካላቸው ለመረዳት ተችሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“በወለጋው ግጭት የሞቱት ከ250 ይበልጣሉ” አቶ ቡልቻ ደመቅሣ

“የሞቱት ከ100 አይበልጡም፣ ጥፋተኞች እየተያዙ ነው» የፌ/ጉ/ሚ/ር ሲራጅ ፊርጌሳ

Ethiopia Zare (ሰኞ ሰኔ 2 ቀን 2000 ዓ.ም. June 9, 2008)፦ በምዕራብ ወለጋ በተነሳው ግጭት የሞቱ ሰዎች ብዛት 250 እንደሆነ የተከበሩ አቶ ቡልቻ ደመቅሣ (የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ሊቀመንበር) ለፓርላማው ገለፁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋና ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ በሎንዶን ክፍል ፪

"ኢህአዴግ ከዚህ በኋላ አምስት ዓመት ከቆየ በእሱ ጥንካሬ ሳይሆን በእኛ ድክመት ነው" ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

Ethiopia Zare (እሁድ ሰኔ 1 ቀን 2000 ዓ.ም. June 8, 2008)፦ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋና ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ በዛሬው ዕለት በሎንዶን ከህዝብ ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ከተሰብሳቢው ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሾች ሰጥተዋል። በዚህ ህዝባዊ ውይይት ላይ ከህዝብ የቀረቡትን ጥያቄዎችና የተሰጡትን ምላሾች በድምፅ እንደሚከተለው አቅርበነዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...